unfoldingWord 34 - ኢየሱስ ሌሎች ታሪኮችን አስተማረ

unfoldingWord 34 - ኢየሱስ ሌሎች ታሪኮችን አስተማረ

Outline: Matthew 13:31-46; Mark 4:26-34; Luke 13:18-21;18:9-14

Script Number: 1234

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ሌሎች ብዙ ታሪኮችን አስተማረ። ለምሳሌ፣ እንዲህ አለ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ሰው በማሳው የዘራትን የሰናፍጭ ዘር ትመስላለች። እርስዋም ከሁሉ ዘር የምታንስ ነች።”

“ነገር ግን የሰናፍጭ ዘር ባደገች ጊዜ አዕዋፍ መጥተው እስኪሰፍሩ ድረስ በአትክልት ቦታ ካሉ ተክሎች ሁሉ ትበልጣለች።

ኢየሱስ ሌላ ታሪክ ተናገረ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ሴት ወስዳ ሁሉ እስኪቦካ ድረስ ከዱቄት ጋር የለወሰችው እርሾ ትመስላለች።

“ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ሰው በእርሻ ውስጥ የሸሸገው መዝገብ ትመስላለች። ሌላ ሰው መዝገቡን አገኘውና እንደ ገና ቀበረው። በጣም በደስታ ተሞልቶ ነበርና ሄዶ ያለውን ነገር ሁሉ ሸጠና በገንዘቡ እርሻውን ገዛው።”

“ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ዋጋዋ እጅግ ውድ የሆነ ዕንቊ ትመስላለች። የዕንቊ ነጋዴ ባገኛት ጊዜ ያለውን ነገር ሁሉ ሸጠና ገዛት።”

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ በራሳቸው መልካም ሥራ ለሚታመኑና ሌሎችን ለሚንቁ አንዳንድ ሰዎች ታሪክ ተናገረ። “ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ። አንዱ ቀረጥ ሰብሳቢ ሲሆን፣ ሌላው የሃይማኖት መሪ ነበር” አለ።

“የሃይማኖት መሪው እንዲህ ብሎ ጸለየ፣ ‘እግዚአብሔር ሆይ፣ እንደ ሌሎች ሰዎች ሁሉ፣ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፣ እንደዚህ ቀረጥ ሰብሳቢ ስላልሆንኩ አመሰግንሃለሁ።”

“ለምሳሌ፣ እኔ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጾማለሁ፣ ከማገኘውም ገንዘብና ንብረት ሁሉ ከዐሥር አንድ አወጣለሁ።’”

“ቀረጥ ሰብሳቢው ግን ከሃይማኖት መሪው ራቅ ብሎ ቆመ፣ ወደ ሰማይ እንኳ አልተመለከተም። በዚህ ፈንታ፣ ደረቱን በእጁ እየመታ፣ ‘እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔ ኃጢአተኛ ስለ ሆንኩ እባክህን ማረኝ።’”

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ እግዚአብሔር የቀረጥ ሰብሳቢውን ጸሎት ሰማና ጻድቅ ነህ አለው። የሃይማኖት መሪውን ጸሎት ግን አልወደደም። እግዚአብሔር ራሱን ከፍ የሚያደርገውን ሁሉ ያዋርዳል፣ ራሱን የሚያዋርደውን ግን ከፍ ያደርጋል።’

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons