unfoldingWord 34 - ኢየሱስ ሌሎች ታሪኮችን አስተማረ

unfoldingWord 34 - ኢየሱስ ሌሎች ታሪኮችን አስተማረ

Raamwerk: Matthew 13:31-46; Mark 4:26-34; Luke 13:18-21;18:9-14

Skripnommer: 1234

Taal: Amharic

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bybelaanhaling: Paraphrase

Status: Approved

Skrips is basiese riglyne vir vertaling en opname in ander tale. Hulle moet so nodig aangepas word dat hulle verstaanbaar en relevant is vir elke verskillende kultuur en taal. Sommige terme en konsepte wat gebruik word, het moontlik meer verduideliking nodig of selfs heeltemal vervang of weggelaat word.

Skripteks

ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ሌሎች ብዙ ታሪኮችን አስተማረ። ለምሳሌ፣ እንዲህ አለ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ሰው በማሳው የዘራትን የሰናፍጭ ዘር ትመስላለች። እርስዋም ከሁሉ ዘር የምታንስ ነች።”

“ነገር ግን የሰናፍጭ ዘር ባደገች ጊዜ አዕዋፍ መጥተው እስኪሰፍሩ ድረስ በአትክልት ቦታ ካሉ ተክሎች ሁሉ ትበልጣለች።

ኢየሱስ ሌላ ታሪክ ተናገረ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ሴት ወስዳ ሁሉ እስኪቦካ ድረስ ከዱቄት ጋር የለወሰችው እርሾ ትመስላለች።

“ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ሰው በእርሻ ውስጥ የሸሸገው መዝገብ ትመስላለች። ሌላ ሰው መዝገቡን አገኘውና እንደ ገና ቀበረው። በጣም በደስታ ተሞልቶ ነበርና ሄዶ ያለውን ነገር ሁሉ ሸጠና በገንዘቡ እርሻውን ገዛው።”

“ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ዋጋዋ እጅግ ውድ የሆነ ዕንቊ ትመስላለች። የዕንቊ ነጋዴ ባገኛት ጊዜ ያለውን ነገር ሁሉ ሸጠና ገዛት።”

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ በራሳቸው መልካም ሥራ ለሚታመኑና ሌሎችን ለሚንቁ አንዳንድ ሰዎች ታሪክ ተናገረ። “ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ። አንዱ ቀረጥ ሰብሳቢ ሲሆን፣ ሌላው የሃይማኖት መሪ ነበር” አለ።

“የሃይማኖት መሪው እንዲህ ብሎ ጸለየ፣ ‘እግዚአብሔር ሆይ፣ እንደ ሌሎች ሰዎች ሁሉ፣ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፣ እንደዚህ ቀረጥ ሰብሳቢ ስላልሆንኩ አመሰግንሃለሁ።”

“ለምሳሌ፣ እኔ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጾማለሁ፣ ከማገኘውም ገንዘብና ንብረት ሁሉ ከዐሥር አንድ አወጣለሁ።’”

“ቀረጥ ሰብሳቢው ግን ከሃይማኖት መሪው ራቅ ብሎ ቆመ፣ ወደ ሰማይ እንኳ አልተመለከተም። በዚህ ፈንታ፣ ደረቱን በእጁ እየመታ፣ ‘እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔ ኃጢአተኛ ስለ ሆንኩ እባክህን ማረኝ።’”

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ እግዚአብሔር የቀረጥ ሰብሳቢውን ጸሎት ሰማና ጻድቅ ነህ አለው። የሃይማኖት መሪውን ጸሎት ግን አልወደደም። እግዚአብሔር ራሱን ከፍ የሚያደርገውን ሁሉ ያዋርዳል፣ ራሱን የሚያዋርደውን ግን ከፍ ያደርጋል።’

Verwante inligting

Woorde van Lewe - GRN het oudio-evangelieboodskappe in duisende tale wat Bybelgebaseerde boodskappe bevat oor verlossing en Christelike lewe.

Gratis aflaaie - Hier vind u al die belangrikste GRN boodskap skrips in verskeie tale, plus prente en ander verwante materiaal, wat beskikbaar is om af te laai.

Die GRN Oudiobiblioteek - Evangelistiese en basiese Bybelonderrigmateriaal wat geskik is vir die behoefte en kultuur van die mense in 'n verskeidenheid style en formate.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons