unfoldingWord 32 - ኢየሱስ ርኵስ መንፈስ የያዘውን ሰውና የታመመችውን ሴት ፈወሰ

unfoldingWord 32 - ኢየሱስ ርኵስ መንፈስ የያዘውን ሰውና የታመመችውን ሴት ፈወሰ

Outline: Matthew 8:28-34; 9:20-22; Mark 5; Luke 8:26-48

Script Number: 1232

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

አንድ ቀን ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ሐይቁን አቋርጠው የጌርጌሴኖን ሰዎች ወደሚኖሩበት አካባቢ ሄዱ።

ወደ ሐይቁ ማዶ በደረሱ ጊዜ ርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ሮጦ ወደ ኢየሱስ መጣ።

ይህ ሰው ማንም ሊቈጣጠረው የማይችል እጅግ ብርቱ ነበረ። ሰዎች እጆቹንና እግሮቹን እንኳ በሰንሰለት አስረውት ነበር፣ ነገር ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ ነበር።

ሰውዬው በአካባቢው ባሉ መቃብሮች መካከል ይኖር ነበር። ይህ ሰው ቀኑንና ሌሊቱን ሁሉ ይጮኽ ነበር። ልብስ አይለብስም ነበር፣ ሰውነቱንም በተደጋጋሚ በድንጋይ ይቧጭር ነበር።

ሰውዬው ወደ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ፣ በፊቱ በጉልበቱ ወድቆ ሰገደለት። ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ከዚህ ሰው ውጣ!” አለው።

ርኵስ መንፈሱ ያለበት ሰው ከፍ ባለ ድምፅ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፣ ከእኔ ምን ትፈልጋለህ? እባክህን አታሠቃየኝ!" ብሎ ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ። ከዚያም ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው” አለና መለሰ። (“ሌጌዎን” በሮማ ጦር ሠራዊት ብዙ ሺህ ወታደሮችን የያዘ ክፍል ነበር።)

ርኵሳን መናፍስቱ፣ “እባክህን ከዚህ አካባቢ አታርቀን!” ብለው ለመኑት። በአቅራቢያው ባለ ኮረብታ ላይ የእሪያ መንጋ ተሰማርቶ ነበር። ስለዚህ ርኵሳን መናፍስቱ ኢየሱስን፣ “እባክህን በዚህ ፈንታ ወደ እሪያዎቹ ስደደን!” ብለው ለመኑት። ኢየሱስ፣ “ሂዱ!” አላቸው።

ርኵሳን መናፍስቱ ከሰውዬው ወጡና ወደ እሪያዎቹ ገቡ። እሪያዎቹ ከአፋፉ ቊልቊል ሮጡና በሐይቁ ሰጠሙ። በመንጋው 2,000 ያህል እሪያዎች ነበሩ።

እሪያዎቹን ይጠብቁ የነበሩት ሰዎች የሆነውን ነገር ባዩ ጊዜ ወደ ከተማ ሮጡና ኢየሱስ ያደረገውን ነገር ላገኙት ሰው ሁሉ ተናገሩ። የከተማው ሰዎች መጡና ርኵሳን መናፍስት የነበሩበትን ሰው ዐዩ። ልብሱን ለብሶ እንደ ጤናማ ሰው ሆኖ በጸጥታ ተቀምጦ ነበር።

ሰዎቹ በጣም ፈርተው ነበርና ኢየሱስን እንዲሄድ ጠየቁት። ስለዚህ ኢየሱስ ጀልባ ውስጥ ገባና ለመሄድ ተዘጋጀ። ርኵን መናፍስት የነበሩበት ሰው ከኢየሱስ ጋር ለመሄድ ልመና አቀረበ።

ነገር ግን ኢየሱስ፣ “አይደለም፣ ወደ ቤትህ ሄደህ እግዚአብሔር ስላደረገልህ ነገር ሁሉና እንዴት እንደ ማረህ ለወዳጆችህና ለቤተ ሰብህ እንድትነግር እፈልጋለሁ” አለው።

ስለዚህ ሰውዬው ሄደና ኢየሱስ ስላደረገለት ነገር ለሁሉም ሰው ተናገረ። ታሪኩን የሰማ ሰው ሁሉ በአድናቆትና በአግራሞት ተሞላ።

ኢየሱስ ወደ ሐይቁ ማዶ ተመለሰ። እዚያ በደረሰ ጊዜ ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ተሰበሰቡና አጨናነቁት። በሕዝቡ መካከል ለዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት ነበረች። እንዲፈውሱአት ገንዘብዋን ሁሉ ለሐኪሞች ከፍላ ነበር፣ ነገር ግን ባሰባት።

ኢየሱስ ብዙ በሽተኞችን እንደ ፈወሰ ሰምታ ነበርና፣ “የኢየሱስን ልብስ ብቻ ብዳስስ ያኔ እኔም እንደምፈወስ እርግጠኛ ነኝ!” ብላ ዐሰበች። ስለዚህ ከኢየሱስ ኋላ መጣችና ልብሱን ዳሰሰች። ልብሱን እንደ ዳሰሰች ወዲያውኑ ደምዋ ቆመ!

ወዲያውኑ፣ ኢየሱስ ኃይል ከእርሱ እንደ ወጣ ዐወቀ። ስለዚህ ወደ ኋላ ዞረና፣ “ማን ነው የዳሰሰኝ?” ብሎ ጠየቀ። ደቀ መዛሙርቱ፣ “በዙሪያህ የተሰበሰቡና የሚያጋፉህ ብዙ ሰዎች አሉ። ‘ስለ ምን ማን ዳሰሰኝ’ ብለህ ትጠይቃለህ?” ብለው መለሱለት።

ሴቲቱ እየተንቀጠቀጠችና በጣም እየፈራች በኢየሱስ ፊት ተደፋች። ከዚያም ያደረገችውን፣ እንዲሁም የተፈወሰች መሆንዋን ነገረችው። ኢየሱስ፣ “እምነትሽ አድኖሻል። በሰላም ሂጂ” አላት።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons