unfoldingWord 38 - ኢየሱስ ተላልፎ ተሰጠ

unfoldingWord 38 - ኢየሱስ ተላልፎ ተሰጠ

Esquema: Matthew 26:14-56; Mark 14:10-50; Luke 22:1-53; John 18:1-11

Número de guión: 1238

Idioma: Amharic

Audiencia: General

Tipo: Bible Stories & Teac

Propósito: Evangelism; Teaching

Citación Biblica: Paraphrase

Estado: Approved

Los guiones son pautas básicas para la traducción y grabación a otros idiomas. Deben adaptarse según sea necesario para que sean comprendidas y relevantes para cada cultura e idioma diferentes. Algunos términos y conceptos utilizados pueden necesitar más explicación o incluso ser reemplazados o omitidos por completo.

Guión de texto

አይሁድ በያመቱ የፋሲካን በዓል ያከብሩ ነበር። ይህም በዓል ከብዙ ምእት ዓመታት በፊት እግዚአብሔር ቅድማያቶቻቸውን በግብፅ ከነበረው ባርነት እንዴት እንዳዳናቸው የሚከበር ነበር። ኢየሱስ መጀመሪያ በይፋ መስበኩንና ማስተማሩን ከጀመረ ከሦስት ዓመት ገደማ በኋላ፣ ይህን ፋሲካ በኢየሩሳሌም ከእነርሱ ጋር ሊያከብር እንደ ፈለገ፣ በዚያም እንደሚገደል ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው።

ከኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ይሁዳ ተብሎ የሚጠራ ሰው ነበር። ይሁዳ የሐዋርያቱ የገንዘብ ከረጢት ኃላፊ ነበር፣ ነገር ግን ገንዘብ ይወድ ነበርና ብዙ ጊዜ ከከረጢቱ ውስጥ ገንዘብ ይሰርቅ ነበር። ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም ከደረሱ በኋላ፣ ይሁዳ ወደ አይሁድ መሪዎች ሄደና ኢየሱስን በገንዘብ አሳልፎ ሊሰጣቸው ተስማማ። ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን የአይሁድ መሪዎች እንደ ካዱና ሊገድሉት ያሤሩ እንደ ነበር ዐወቀ።

የአይሁድ መሪዎች በሊቀ ካህናቱ እየተመሩ፣ ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጣቸው ለይሁዳ ሠላሳ ብር ከፈሉት። ልክ ነቢያት እንደ ተነበዩት ይህ ሆነ። ይሁዳ ተስማማ፣ ገንዘቡንም ይዞ ሄደ። ኢየሱስን እንዲይዙት ሊረዳቸው አጋጣሚ መፈለግ ጀመረ።

በኢየሩሳሌም፣ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ፋሲካን አከበረ። በፋሲካው ምግብ ጊዜ ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ቈረሰ። እንዲህም አለ፣ “እንካችሁ ይህንን ብሉ። ይህ ስለ እናንተ የተሰጠ ሥጋዬ ነው። ይህንን ለመታሰቢያዬ አድርጉት።” በዚህ ዓይነት ኢየሱስ ሥጋው ስለ እርሱ እንደሚሠዋ ነገራቸው።

ከዚያም ኢየሱስ ጽዋን አንሣና፣ “ይህንን ጠጡ። ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የዐዲስ ኪዳን ደሜ ነው። ይህንን በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ለመታሰቢያዬ አድርጉት።”

ከዚያም ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ “ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጠኛል” አላቸው። ደቀ መዛሙርቱ ደነገጡ፣ እንዲህ ያለ ነገር ማን ያደርጋል ብለውም ጠየቁ። ኢየሱስ፣ “ይህንን ቊራሽ እንጀራ የምሰጠው ሰው እኔን አሳልፎ ይሰጠኛል” አለ። ከዚያ በኋላ እንጀራውን ለይሁዳ ሰጠው።

ይሁዳ እንጀራውን ከተቀበለ በኋላ፣ ሰይጣን ገባበት። ይሁዳ ኢየሱስን እንዲይዙ የአይሁድ መሪዎችን ሊረዳቸው ሄደ። ጊዜው ማታ ነበር።

ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ እራት ከበሉ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ሄዱ። ኢየሱስ፣ “ዛሬ ማታ ሁላችሁም ትተዉኛላችሁ። ‘እረኛውን እመታለሁ በጎቹም ሁሉ ይበተናሉ’ ተብሎ ተጽፎአል” አለ።

ጴጥሮስ፣ “ሌሎቹ ሁሉ ቢተዉህ እንኳ፣ እኔ ግን አላደርገውም!” ብሎ መለሰ። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ጴጥሮስን እንዲህ አለው፣ “ሰይጣን ሁላችሁንም ሊወስዳችሁ ይፈልጋል፣ ነገር ግን ጴጥሮስ እምነትህ እንዳይደክም ጸልዬልሃለሁ። እንደዚያም ሆኖ ግን ዛሬ ማታ ዶሮ ከመጮኹ በፊት እንደማታውቀኝ እንኳ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ።”

በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስ፣ “መሞት ቢኖርብኝ እንኳ፣ ከቶ አልክድህም” አለው። ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ሁሉ ይህንኑ አሉ።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደሚባል ቦታ ሄደ። ኢየሱስ ወደ ፈተና እንዳይገቡ እንዲጸልዩ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ከዚያም ኢየሱስ ብቻውን ሊጸልይ ሄደ።

ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ጸለየ፣ “አባቴ ሆይ፣ ቢቻልስ ይህን የመከራ ጽዋ እንዳልጠጣው አድርግ። ነገር ግን የሰዎች ኃጢአት ይቅር የሚባልበት ሌላ መንገድ ከሌለ፣ ፈቃድህ ይሁን።” ኢየሱስ በጣም ታወከ ላቡም እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ። እግዚአብሔር ሊያበረታታው መልአክ ላከ።

ከእያንዳንዱ የጸሎት ጊዜ በኋላ ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ ተመላለሰ፣ እነርሱ ግን ተኝተው ነበር። ሦስተኛ በተመለሰ ጊዜ ግን፣ “ተነሡ! አሳልፎ የሚሰጠኝ እዚህ ነው” አለ።

ይሁዳ ከአይሁድ መሪዎች፣ ከወታደሮችና ከብዙ ሕዝብ ጋር መጣ። ሰይፍና ዱላ ይዘው ነበር። ይሁዳ ወደ ኢየሱስ መጣና፣ “መምህር ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን” አለው፣ ሳመውም። ይህም የአይሁድ መሪዎች ማንን እንደሚይዙ ምልክት ነበር። ከዚያም ኢየሱስ፣ “ይሁዳ፣ በመሳም አሳልፈህ ትሰጠኛለህን?” አለ።

ወታደሮቹ ኢየሱስን እንደ ያዙት፣ ጴጥሮስ ሰይፉን መዘዘና የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ ቈረጠ። ኢየሱስ፣ “ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ! ይከላከሉልኝ ዘንድ የመላእክት ሠራዊት እንዲልክልኝ አባቴን መጠየቅ እችላለሁ” አለው። ከዚያም ኢየሱስ የሰውዬውን ጆሮ ፈወሰው። ኢየሱስ ከተያዘ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ሸሹ።

Información relacionada

Palabras de Vida - GRN tiene mensajes audios en miles de idiomas que contienen mensajes basados en la Biblia acerca de la salvación y la vida cristiana.

Descargas gratis - Aquí puede encontrar los guiones principales de GRN en varios idiomas y también imágenes y otros materiales relacionados. Todos están disponibles para descargar.

Librería de audio de GRN - Material evangelistico y de enseñanza adecuado a las necesidades y a la cultura en variedad de stilos y formatos

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons