unfoldingWord 19 - ነቢያቱ

unfoldingWord 19 - ነቢያቱ

Outline: 1 Kings 16-18; 2 Kings 5; Jeremiah 38

Script Number: 1219

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

እግዚአብሔር በእስራኤላውያን ታሪክ በሙሉ፣ ነቢያትን ላከላቸው። ከእግዚአብሔር መልእክት ሰሙ ከዚያም የእግዚአብሔርን መልእክት ለሕዝቡ ነገሩአቸው።

አክአብ በእስራኤል መንግሥት ላይ በነገሠ ጊዜ ኤልያስ ነቢይ ነበረ። አክዓብ በኣል ተብሎ የሚጠራ የሐሰት አምላክ እንዲያመልኩ ሕዝቡን ያደፋፈረ ክፉ ሰው ነበር። ኤልያስ ለአክዓብ፣ “እኔ እስከምናገር ድረስ በእስራኤል ዝናብ ወይም ጠል አይኖርም” አለው። ይህ አክዓብን በጣም አስቈጣው።

እግዚአብሔር ሊገድለው ከሚፈልገው ከአክዓብ ለመሸሸግ በምድረ በዳ ወዳለ ወንዝ እንዲሄድ ለኤልያስ ነገረው። በየጠዋቱና በየምሽቱ ወፎች እንጀራና ሥጋ ያመጡለት ነበር። አክዓብና ጦር ሠራዊቱ ኤልያስን ፈለጉት፣ ነገር ግን ሊያገኙት አልቻሉም። ድርቁ በጣም ከባድ ነበርና በመጨረሻ ወንዙ ደረቀ።

ስለዚህ ኤልያስ ወደ አንድ ጐረቤት አገር ሄደ። በዚያች አገር በረሀቡ ምክንያት አንዲት መበለትና ወንድ ልጅዋ ምግብ ሊያልቅባቸው ተቃርበው ነበር። ነገር ግን ኤልያስን ተንከባከቡት፣ እግዚአብሔርም ዱቄቱ ከማድጋ ዘይቱም ከማሰሮ እንዳይጐድል አድርጎ መገባቸው። በረሀቡ ጊዜ ሁሉ ምግብ ነበራቸው። ኤልያስ በዚያ ለአያሌ ዓመታት ተቀመጠ።

ከሦስት ዓመት ተኩል በኋላ ዝናብ የሚያዘንብ መሆኑን ወደ እስራኤል መንግሥት ተመልሶ ለአክዓብ እንዲነግረው እግዚአብሔር ለኤልያስ ነገረው። አክዓብ ኤልያስን ባየው ጊዜ፣ “አንተ ችግር ፈጣሪ፣ መጣህ አይደል!” አለው። ኤልያስ እንዲህ ብሎ መለሰት፣ “ችግር ፈጣሪ አንተ ነህ! እውነተኛውን አምላክ፣ ያህዌን ትተሃል፣ በኣልንም አምልከሃል የእስራኤልን መንግሥት ሕዝብ ሁሉ በቀርሜሎስ ተራራ ላይ ሰብስብ።”

450ዎቹ የበኣል ነቢያትን ጨምሮ የእስራኤል መንግሥት ሕዝብ ሁሉ ወደ ቀርሜሎስ ተራራ መጡ። ኤልያስ ለሕዝቡ፣ “ስንት ጊዜ ዐሳባችሁን ትለውጣላችሁ? እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን አገልግሉ! በኣል አምላክ ቢሆን እርሱን አገልግሉ!” አላቸው።

ከዚያም ኤልያስ ለበኣል ነቢያት፣ “አንድ ወይፈን እረዱና መሥዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡት፣ ነገር ግን እሳት አታንድዱ። እኔም እንደዚሁ አደርጋለሁ። በእሳት የሚመልስ አምላክ እርሱ እውነተኛ አምላክ ነው” አላቸው። ስለዚህ የበኣል ካህናት መሥዋዕት አዘጋጁ ነገር ግን እሳት አላነደዱም።

ከዚያ በኋላ የበኣል ነቢያት “በኣል ሆይ፣ ስማን!” ብለው ወደ በኣል ጸለዩ። ቀኑን ሙሉ ጸለዩ፣ ጮኹ፣ እንዲሁም ሰውነታቸውን በቢላዋ ቈረጡ፣ ነገር ግን መልስ አልነበረም።

በመጨረሻ፣ ኤልያስ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አዘጋጀ። ከዚያም ሥጋው፣ እንጨቱ፣ እንዲሁም በመሠዊያው ዙሪያ ያለው መሬት እንኳ ፍጹም እስኪረጥብ ድረስ ዐሥራት ሁለት ጋን ሙሉ ውሃ በመሥዋዕቱ ላይ እንዲያፈሱ ለሕዝብ ነገራቸው።

ከዚያም ኤልያስ እንዲህ ብሎ ጸለየ፣ “ያህዌ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ፣ አንተ የእስራኤል አምላክ እንደ ሆንክና እኔም አገልጋይህ እንደ ሆንኩ ዛሬ ዐሳየን። አንተ እውነተኛ አምላክ እንደ ሆንክ ይህ ሕዝብ ያውቅ ዘንድ መልስልኝ።”

ወዲያውኑ፣ እሳት ከሰማይ ወደቀና ሥጋውን፣ እንጨቱን፣ ድንጋዩን፣ ቈሻሻውን፣ እንዲሁም በመሠዊያው ዙሪያ የነበረውን ውሃ እንኳ አቃጠለ። ሕዝቡ ይህን ባዩ ጊዜ መሬት ላይ ወደቁና “ያህዌ አምላክ ነው! ያህዌ አምላክ ነው!” አሉ።

ከዚያም ኤልያስ፣ “ከበኣል ነቢያት አንድም እንዳያመልጥ!” አለ። ስለዚህ ሕዝቡ የበኣልን ነቢያት ያዙና ወስደው ገደሉአቸው።

ከዚያ በኋላ ኤልያስ ለንጉሥ አክዓብ፣ “ዝናብ መጥቶአልና ፈጥነህ ወደ ከተማ ተመለስ” አለው። ወዲያውኑ ሰማዩ ጠቈረ፣ ከባድ ዝናብም መዝነብ ጀመረ። ያህዌ ድርቁን አቆመው እውተኛ አምላክ መሆኑንም አረጋገጠ።

ከኤልያስ ዘመን በኋላ፣ እግዚአብሔር ነቢይ እንዲሆን ኤልሳዕ የተባለ ሰውን መረጠ። እግዚአብሔር በኤልሳዕ በኩል ብዙ ተአምራትን አደረገ። ከተአምራቱ አንዱ አስከፊ የቆዳ በሽታ በያዘው የጠላት ጦር ሠራዊት አዛዥ በነበረው ንዕማን ላይ ተከሠተ። ስለ ኤልሳዕ ሰምቶ ነበርና ስለዚህ እንዲፈውሰው ኤልሳዕን ሄዶ ጠየቀው። ኤልሳዕ በዮርዳኖስ ወንዝ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እንዲል ለንዕማን ነገረው።

በመጀመሪያ ንዕማን ተቈጣና ሞኝነት ስለ መሰለው ኤልሳዕ የነገረውን ነገር አላደረገውም። በኋላ ግን ዐሳቡን ለወጠና በዮርዳኖስ ወንዝ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ። በመጨረሻ ከውሃው በወጣ ጊዜ ቆዳው ፍጹም ተፈወሰ! እግዚአብሔር ፈወሰው።

እግዚአብሔር ሌሎች ብዙ ነቢያትን ላከ። ሁላቸውም ጣዖታትን ማምለክ እንዲያቆሙና ለሌሎች ፍትሕንና ምሕረትን ማሳየት እንዲጀምሩ ለሕዝቡ ነገሩአቸው። ነቢያቱ ክፉ መሥራትን ባያቆሙና ለእግዚአብሔር መታዘዝ ባይጀምሩ፣ እግዚአብሔር በበደለኝነት እንደሚፈርድባቸው፣ እንደሚቀጣቸውም ሕዝቡን አስጠነቀቁአቸው።

አብዛኛውን ጊዜ ሕዝቡ ለእግዚአብሔር አልታዘዙም። ብዙውን ጊዜ ለነቢያት የነበራቸው አያያዝ መጥፎ ነበረ፣ አንዳንድ ጊዜም ይገደሉአቸው ነበር። በአንድ ወቅት፣ ነቢዩ ኤርምያስ ደረቅ በሆነ የውሃ ጕድጓድ ውስጥ ተጥሎ በዚያ እንዲሞት ተትቶ ነበር። በጕድጓዱ መጨረሻ በነበረው ጭቃ ውስጥ ገባ፣ ነገር ግን ያኔ ንጉሡ ራራለትና ከመሞቱ በፊት ከጕድጓዱ ጐትተው እንዲያወጡት አገልጋዮቹን አዘዛቸው።

ነቢያቱ ሕዝቡ ቢጡሉአቸውም እንኳ ስለ እግዚአብሔር መናራቸውን ቀጠሉ። ንስሐ ባይገቡ እግዚአብሔር እንደሚያጠፋቸው ሕዝቡን አስጠነቀቁአቸው። ደግሞም የእግዚአብሔር መሲሕ እንደሚመጣ ስለ ሰጠው ተስፋ ለሕዝቡ አስታወሱአቸው።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons