unfoldingWord 11 - ፋሲካ
абрис: Exodus 11:1-12:32
Номер сценарію: 1211
Мову: Amharic
Аудиторія: General
Мета: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
Статус: Approved
Сценарії є основними вказівками для перекладу та запису на інші мови. Їх слід адаптувати, якщо це необхідно, щоб зробити їх зрозумілими та відповідними для кожної окремої культури та мови. Деякі терміни та поняття, які використовуються, можуть потребувати додаткових пояснень або навіть бути замінені чи повністю опущені.
Текст сценарію
እስራኤላውያንን ካልለቀቀ የሰዎችንና የእንስሳትን ተባዕት በኵር ሁሉ እንደሚገድል እግዚአብሔር ፈርዖንን አስጠነቀቀው። ፈርዖን ይህን በሰማ ጊዜ፣ አሁንም ማመንና ለእግዚአብሔር መታዘዝ እምቢ አለ።
እግዚአብሔር በእርሱ ያመነ የማንኛውም ሰው በኵር ወንድ ልጅ ለማዳን መንገድ አዘጋጀ። እያንዳንዱ ቤተ ሰብ ፍጹም የሆነ ጠቦት መርጦ አረደ።
እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡት፣ ሥጋውንም ጠብሰው ያለ እርሾ ከተጋገረው ቂጣ ጋር በፍጥነት እንዲበሉት ነገራቸው። ደግሞ በበሉት ጊዜ ከግብፅ ለመውጣት እንዲዘጋጁ ነገራቸው።
እስራኤላውያን ልክ እግዚአብሔር እንዲያደርጉ እንዳዘዛቸው ሁሉንም ነገር አደረጉ። እኩለ ሌሊት ላይ እግዚአብሔር በመላው ግብፅ አልፎ ወንድ በኵርን ሁሉ ገደለ።
የእስራኤላውያን ቤቶች ሁሉ በሮቻቸው ደም ተቀብተው ነበር፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቹ አለፈ። በቤቶቹ ውስጥ የነበረው ሰው ሁሉ ዳነ። እስራኤላውያን በጠቦቱ ደም ምክንያት ዳኑ።
ግብፃውያን ግን በእግዚአብሔር አላመኑም፣ ትእዛዛቱንም አልፈጸሙም። ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቻቸው አላለፈም። እግዚአብሔር የግብፃውያንን በኵር ወንዶችን ሁሉ ገደለ።
በእስር ቤት ካለው በኵር እስረኛ ጀምሮ እስከ ፈርዖን በኵር ድረስ እያንዳንዱ ግብፃዊ በኵር ወንድ ሞተ። ከጥልቅ ሐዘናቸው የተነሣ በግብፅ የነበሩ ብዙ ሰዎች ያለቅሱና ይጮኹ ነበር።
በዚያው ሌሊት ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “እስራኤላውያንን ይዛችሁ አሁኑኑ ሂዱ!” አላቸው።