Välj ett språk

mic

Dela med sig

Dela länk

QR code for https://globalrecordings.net/script/7787

unfoldingWord 40 - ኢየሱስ ተሰቀለ

unfoldingWord 40 - ኢየሱስ ተሰቀለ

Översikt: Matthew 27:27-61; Mark 15:16-47; Luke 23:26-56; John 19:17-42

Skriptnummer: 1240

Språk: Amharic

Publik: General

Ändamål: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Status: Approved

Skript är grundläggande riktlinjer för översättning och inspelning till andra språk. De bör anpassas efter behov för att göra dem begripliga och relevanta för olika kulturer och språk. Vissa termer och begrepp som används kan behöva mer förklaring eller till och med ersättas eller utelämnas helt.

Manustext

ወታደሮቹ በኢየሱስ ላይ ከዘበቱ በኋላ፣ ሊሰቅሉት ወሰዱት። የሚሞትበትን እንዲሸከም አደረጉት።

ወታደሮቹ ኢየሱስን “የራስ ቅል” ተብሎ ወደሚጠራ ስፍራ አመጡትና እጆቹንና እግሮቹን በመስቀል ላይ ጠረቁአቸው። ኢየሱስ ግን፣ “አባት ሆይ፣ የሚያደርጉትን ዐያውቁምና ይቅር በላቸው” አለ። ጲላጦስ፣ በምልክት ላይ፣ “የአይሁድ ንጉሥ” ብለው እንዲጽፉና ከኢየሱስ ራስ በላይ በመስቀሉ ላይ እንዲያኖሩት አዘዘ።

ወታደሮቹ በኢየሱስ ልብስ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ። ይህንን ባደረጉበት ጊዜ፣ “ልብሶቼን ተከፋፈሉ፣ በልብሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ” የሚለውን ትንቢት ፈጸሙ።

ኢየሱስ በሁለት ወንበዴዎች መካከል ተሰቀለ። አንደኛው በኢየሱስ ላይ ዘበተበት፣ ሌላኛው ግን፣ “አንተ እግዚአብሔርን አትፈራም? እኛ በደለኞች ነን፣ ይህ ሰው ግን በደል የለበትም” አለ። ከዚያም ኢየሰስን፣ “እባክህን በመንግሥትህ ዐስበኝ” አለው። ኢየሱስ፣ “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” ብሎ መለሰለት።

የአይሁድ መሪዎችና በሕዝቡ መካከል የነበሩ ሌሎች ሰዎች በኢየሱስ ላይ ተዘባበቱበት። “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል ላይ ውረድና ራስህን አድን! ከዚያ በኋላ እናምንብሃለን” አሉት።

በዚያን ጊዜ እኩለ ቀን ቢሆንም፣ በአካባቢው ሁሉ ላይ ሰማዩ ፍጹም ጨለማ ሆነ። ከእኩለ ቀን እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ እንደ ጨለመ ቆየ።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ፣ “ተፈጸመ! አባት ሆይ፣ ነፍሴን በእጅህ እሰጣለሁ” ብሎ ጮኸ። ከዚያም ራሱን አዘነበለና መንፈሱን ሰጠ። በሞተ ጊዜ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፣ በቤተ መቅደስ የነበረው ሕዝቡን ከእግዚአብሔር መገኘት የለየው ትልቁ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀደደ።

ኢየሱስ በሞቱ በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲመጡ ለሰዎች መንገድ ከፈተላቸው። ኢየሱስን ይጠብቅ የነበረው ወታደር የሆነውን ሁሉ ባየ ጊዜ፣ “በእርግጥ ይህ ሰው በደል የለበትም። የእግዚአብሔር ልጅ ነው” አለ።

በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን ያመኑ ሁለት የአይሁድ መሪዎች፣ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የኢየሱስን ሥጋ እንዲሰጣቸው ጲላጦስን ለመኑት። ሥጋውን በጨርቅ ገነዙትና ከአለት በተወቀረ መቃብር አኖሩት። ከዚያም ክፍቱን ስፍራ ለመዝጋት ከመቃብሩ ፊት ለፊት ትልቅ ድንጋይ አንከባለሉ።

Relaterad information

Livets ord - Ljudevangeliebudskap på tusentals språk som innehåller bibelbaserade budskap om frälsning och kristet liv.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons