unfoldingWord 18 - የተከፈለው መንግሥት
概要: 1 Kings 1-6; 11-12
スクリプト番号: 1218
言語: Amharic
観客: General
目的: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
状態: Approved
スクリプトは、他の言語への翻訳および録音の基本的なガイドラインです。スクリプトは、それぞれの異なる文化や言語で理解しやすく、関連性のあるものにするために、必要に応じて適応させる必要があります。使用される用語や概念の中には、さらに説明が必要な場合や、完全に置き換えたり省略したりする必要がある場合もあります。
スクリプトテキスト
ከብዙ ዓመታት በኋላ፣ዳዊት ሞተ፣ ልጁ ሰሎሞንም በእስራኤል ላይይገዛ ጀመር። እግዚአብሔር ለሰሎሞን ተናገረውና በይበልጥ ምን እንደሚፈልግ ጠየቀው። ሰሎሞን ጥበብን በለመነጊዜ፣ በዓለም ላይእጅግ በጣም ጠቢብ ሰው አደረገው። ሰሎሞን ብዙ ነገሮችን ተማረናበጣም ጠቢብ ፈራጅ ሆነ። ደግሞም እግዚአብሔርበጣም ባለ ጠጋ አደረገው።
ሰሎሞን በኢየሩሳሌም አባቱ ዳዊት ያቀደውንና ለግንባታው የሚያስፈልጉ ነገሮች የሰበሰበለትን ቤተ መቅደሱን ሠራ። አሁን ሕዝቡ በመገናኛው ድንኳ ፈንታ በቤተ መቅደሱ እግዚአብሔርን አመለኩ መሥዋዕትንም አቀረቡለት። እግዚአብሔር መጥቶ በቤተ መቅደሱ ተገኘ፣ በዚያም ከሕዝቡ ጋር ኖረ።
ነገር ግን ሰሎሞን ከሌሎች አገሮች የሆኑ ሴቶችን ወደደ። ከሞላ ጐደል 1000 የሚሆኑ ብዙ ሴቶችን በማግባት ለእግዚአብሔር አልታዘዘም! ከእነዚህ ሴቶች ብዙዎቹ ከውጪ አገሮች መጡ፣ ጣዖቶቻቸውን አመጡና እነርሱኑ ማምለካቸውን ቀጠሉ። ሰሎሞን በሸመገለ ጊዜ፣ እርሱም ደግሞ የእነርሱን አማልክት አመለከ።
እግዚአብሔር በሰሎሞን ላይ ተቈጣ፣ ሰሎሞን ባለመታመኑ እንደ መቀጣጫ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤልን ሕዝብ ወደ ሁለት መንግሥታት እንደሚከፍል ተናገረ።
ሰሎሞን ከሞተ በኋላ ልጁ ሮብዓም ነገሠ። ሮብዓም ሞኝ ነበረ። የእስራኤል ሕዝብ በሙሉ ንጉሥነቱን ሊያጸድቁለት ተሰብስበው መጡ። ሰሎሞን ብዙ ከባድ ሥራ እንዳሠራቸውና ብዙ ግብር እንዳስከፈላቸው ለሮብዓም ቅሬታቸውን ተናገሩ።
ሮብዓም በሞኝነት እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፣ “አባቴ ሰሎሞን ከባድ ሥራ አሠርቶናል ብላችሁ ዐስባችኋል፣ ነገር ግን እኔ ከእርሱ የባሰ ከባድ ሥራ አሠራችኋለሁ፣ ከእርሱ የባሰም በኃይል እቀጣችኋለሁ።”
ዐሥሩ የእስራኤል ሕዝብ ነገዶች በሮብዓም ላይ ዓመፁ። ሁለት ነገዶች ብቻ ለእርሱ ባላቸው ታማኝነት ቀጠሉ። እነዚህ ሁለት ነገዶች የይሁዳ መንግሥት ሆኑ።
በሮብዓም ላይ ያመፁት ሌሎቹ ዐሥር የእስራኤል ሕዝብ ነገዶች ኢዮርብዓም የተባለውን ሰው ንጉሣቸው አድርገው ሾሙት። በምድሪቱ ሰሜናዊ ክፍል መንግሥታቸውን አቋቋሙ የእስራኤል መንግሥት ተብለውም ተጠሩ።
ኢዮርብዓም በእግዚአብሔር ላይ ዓመፀና ሕዝቡ ኃጢአት እንዲሠሩ አደረገ። በይሁዳ መንግሥት ባለው ቤተ መቅደስ እግዚአብሔርን በማምለክ ፈንታ ሕዝቡ ያመልኩአቸው ዘንድ ሁለት ጣዖታትን ሠራላቸው።
የይሁዳና የእስራኤል መንግሥታት ጠላቶች ሆኑና ብዙ ጊዜ እርስ በርስ ተዋጉ።
በዐዲሲቱ የእስራኤል መንግሥት፣ ነገሥታቱ ሁሉ ክፉዎች ነበሩ። ከእነዚህ ነገሥታት አብዛኞቹ፣ በእነርሱ ቦታ መንገሥ በፈለጉ ሌሎች እስራኤላውያን ተገደሉ።
ነገሥታቱ ሁሉና አብዛኞቹ የእስራኤል መንግሥት ሕዝብ ጣዖትን አመለኩ። የጣዖት አምልኮአቸው ብዙውን ጊዜ ግብረ ገብነት የጐደለው የግብረ ሥጋ ግንኙነትና አንዳንድ ጊዜ ልጆችን መሠዋትን ያካተተ ነበር።
የይሁዳ ነገሥታት የዳዊት ዝርያዎች ነበሩ። ከእነዚህ ነገሥታት አንዳንዶቹ በትክክል የገዙና እግዚአብሔርን ያመለኩ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን አብዛኞቹ ነገሥታት ክፉዎችና ብልሹዎች ነበሩ፣ ጣዖታትንም ያመልኩ ነበር። አንዳንዶቹ ነገሥታት ልጆቻቸውን እንኳ ለሐሰት አማልክት ሠውተዋል። ደግሞም አብዛኞቹ የይሁዳ ሕዝብ በእግዚአብሔር ላይ ዓመፁ ሌሎች አማልክትንም አመለኩ።