unfoldingWord 47 - ጳውሎስና ሲላስ በፊልጵስዩስ

unfoldingWord 47 - ጳውሎስና ሲላስ በፊልጵስዩስ

Esquema: Acts 16:11-40

Número de guión: 1247

Idioma: Amharic

Audiencia: General

Tipo: Bible Stories & Teac

Propósito: Evangelism; Teaching

Citación Biblica: Paraphrase

Estado: Approved

Los guiones son pautas básicas para la traducción y grabación a otros idiomas. Deben adaptarse según sea necesario para que sean comprendidas y relevantes para cada cultura e idioma diferentes. Algunos términos y conceptos utilizados pueden necesitar más explicación o incluso ser reemplazados o omitidos por completo.

Guión de texto

ሳውል በሮማ የንጉሠ ነገሥት ግዛት ሁሉ በሚጓዝበት ጊዜ፣ ሮማዊ ስሙን “ጳውሎስ”ን መጠቀም ጀመረ። አንድ ቀን ጳውሎስና ጓደኛው ሲላስ ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች ሊያውጁ ወደ ፊልጵስዩስ ከተማ ሄዱ። ሰዎች ሊጸልዩ ወደ ተሰበሰቡበት ከከተማይቱ ውጭ በወንዙ አጠገብ ወዳለ ስፍራ ሄዱ። በዚያ ነጋዴ የነበረች ልድያ የሚሉአት አንዲት ሴት አገኙ። እርስዋ እግዚአብሔርን ትወድና ታመልክ ነበር።

ስለ ኢየሱስ የሚነገረውን መልእክት እንድታምን እግዚአብሔር የልድያን ልብ ከፈተላት፤ እርስዋና ቤተ ሰብዋ ተጠመቁ፣ በቤትዋ እንዲኖሩ ጳውሎስንና ሲላስን ጋበዘቻቸው፣ ስለዚህ እነርሱ ከእርስዋና ከቤተ ሰብዋ ጋር ኖሩ።

ጳውሎስና ሲላስ ብዙ ጊዜ በጸሎት ስፍራ ከሰዎች ጋር ይገናኙ ነበር። በየዕለቱ ወደዚያ ሲሄዱ ጋኔን የያዛት አንዲት ባሪያ ልጃገረድ ትከተላቸው ነበር። እርሷም በዚህ ጋኔን አማካይነት ስለ መጪው ጊዜ ለሰዎች ትተነብይላቸው ነበር፣ ስለዚህ በጥንቈላ ለጌቶችዋ ብዙ ገንዘብ ታስገኝ ነበር።

ባሪያዪቱ ልጃገረድ እነርሱ ሲዘዋወሩ እየተከተለቻቸው፣ “እነዚህ ሰዎች የልዑል እግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው። የመዳንን መንገድ ይነግሩአችኋል!” በማለት መጮህዋን ቀጠለች። ጳውሎስ እስኪቈጣ ድረስ ይህንን ደጋግማ አደረገች።

በመጨረሻም አንድ ቀን ባሪያዪቱ ልጃገረድ መጮኽ በጀመረች ጊዜ ጳውሎስ ወደ እርስዋ ዘወር አለና በእርስዋ የነበረውን ጋኔን፣ “በኢየሱስ ስም፣ ከእርስዋ ውጣ” አለው። ወዲያውኑ ጋኔኑ ለቀቃት።

የባሪያዪቱ ልጃገረድ ጌቶች የነበሩት ሰዎች በጣም ተቈጡ! ያለ ጋኔኑ ባሪያዪቱ ልጅ ስለ ሰዎች መጪ ጊዜ መናገር እንደማትችል ዐወቁ። ይህም ሰዎች የሚደርስባቸውን ነገር ትነግራቸው ዘንድ ስለማትችል ለጌቶችዋ ገንዘብ አይከፍሉም ማለት ነው።

ስለዚህ የባሪያዪቱ ልጃገረድ ጌቶች ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ሮማ ባለ ሥልጣናት ወሰዱአቸው፣ እነርሱም ደብድበው ወደ እስር ቤት ጣሉአቸው።

እነርሱም ጳውሎስንና ሲላስን በእስር ቤት ውስጠኛ ክፍል አሰሩአቸው እግሮቻቸውን እንኳ ከግንድ ጋር አሰሩአቸው። ሆኖም ግን እከለ ሌሊት ላይ ለእግዚአብሔር የምስጋና መዝሙር ዘመሩ።

በድንገት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ሆነ! የእስር ቤቱ በሮች ሁሉ ወለል ብለው ተከፈቱ፣ የእስረኞቹ ሁሉ ሰንሰለቶችም ረገፉ።

የእስር ቤቱ ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቃ፣ የእስር ቤቱ በሮች ሁሉ መከፈታቸውን ባየ ጊዜ ፈራ! እስረኞቹ ሁሉ ያመለጡ መሰለው፣ ስለዚህ ራሱን ለመግደል ዐሰበ። (እስረኞቹ እንዲያመልጡ ካደረገ የሮማ ባለ ሥልጣናት እንደሚገድሉት ዐወቀ።) ነገር ግን ጳውሎስ ዐየውና፣ “ተው! ራስህን አትጕዳ። ሁላችንም እዚህ አለን” ብሎ ጮኸበት።

የእስር ቤቱ ጠባቂ ወደ ጳውሎስና ሲላስ እየመጣ እያለ ተንቀጠቀጠና፣ “እድን ዘንድ ምን ላድርግ?” ብሎ ጠየቀ። ጳውሎስ፣ “በጌታ በኢየሱስ እመን፣ አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ” ብሎ መለሰለት። ከዚያም የእስር ቤት ጠባቂው ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ቤቱ ወሰዳቸውና ቊስላቸውን አጠበላቸው። ጳውሎስ በቤቱ ለነበሩት ሁሉ ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች ሰበከላቸው።

የእስር ቤት ጠባቂውና መላው ቤተ ሰቡ በኢየሱስ አምነው ተጠመቁ። ከዚያም የእስር ቤት ጠባቂው ለጳውሎስና ለሲላስ ምግብ አቀረበላቸውና በአንድነት ደስ አላቸው፡

በማግስቱ የፊልጵስዩስ መሪዎች ጳውሎስና ሲላስን ከእስር ቤት ፈቱአቸውና ከፊልጵስዩስ እንዲሄዱ ጠየቁአቸው። ጳውሎስና ሲላስ ልድያንና አንዳንድ ሌሎች ወዳጆችን ጐበኙና ከተማይቱን ለቀው ሄዱ። ስለ ኢየሱስ የሚናገረው የምሥራች መስፋፋቱን ቀጠለ ቤተ ክርስቲያንም ማደግዋን ቀጠለች።

ጳውሎስና ሌሎች ክርስቲያን መሪዎች ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች እየሰበኩና እያስተማሩ ወደ ብዙ ከተሞች ተጓዙ። ደግሞም በአብያተ ክርስቲያናቱ ላሉ አማኞች ሊያበረታቱአቸውና ሊያስተምሩአቸው ብዙ መልእክቶችን ጻፉላቸው። ከእነዚህ መልእክቶች አንዳንዶቹ በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉት መጻሕፍት ሆኑ።

Información relacionada

Palabras de Vida - GRN tiene mensajes audios en miles de idiomas que contienen mensajes basados en la Biblia acerca de la salvación y la vida cristiana.

Descargas gratis - Aquí puede encontrar los guiones principales de GRN en varios idiomas y también imágenes y otros materiales relacionados. Todos están disponibles para descargar.

Librería de audio de GRN - Material evangelistico y de enseñanza adecuado a las necesidades y a la cultura en variedad de stilos y formatos

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?