unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

Esquema: Luke 10:25-37

Número de guión: 1227

Idioma: Amharic

Audiencia: General

Tipo: Bible Stories & Teac

Propósito: Evangelism; Teaching

Citación Biblica: Paraphrase

Estado: Approved

Los guiones son pautas básicas para la traducción y grabación a otros idiomas. Deben adaptarse según sea necesario para que sean comprendidas y relevantes para cada cultura e idioma diferentes. Algunos términos y conceptos utilizados pueden necesitar más explicación o incluso ser reemplazados o omitidos por completo.

Guión de texto

አንድ ቀን አንድ የአይሁድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ወደ ኢየሱስ መጣ፣ “መምህር ሆይ፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” አለው። ኢየሱስ፣ “በእግዚአብሔር ሕግ የተጻፈው ምንድን ነው?” ብሎ መለሰለት።

ሕግ ዐዋቂው የእግዚአብሔርሕግ፣ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም ዐሳብህም ውደድ። ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ” ይላል ብሎ መለሰ። ኢየሱስ፣ “ትክክል ነህ! ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ” አለው።

ነገር ግን ሕግ ዐዋቂው ጻድቅ መሆኑን ለማረጋገጥ ፈለገ፣ ስለዚህ፣ “ባልንጀራዬ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀ።

ኢየሱስ ታሪክ በመናገር ለሕግ ዐዋቂው መለሰለት። “ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ይጓዝ የነበረ አንድ አይሁዳዊ ነበረ።”

“ሰውዬው በመጓዝ ላይ እያለ ወንበዴዎች ያዙት። የነበረውን ነገር ሁሉ ወሰዱበትና እስኪሞት ድረስ ደበደቡት። ከዚያም ሄዱ።”

ከዚያ በኋላ ወዲያውኑ አንድ አይሁዳዊ ካህን በዚያ መንገድ ይጓዝ ነበር። ይህ የሃይማኖት መሪ የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው ባየ ጊዜ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ሄደ፣ ርዳታ የፈለገውን ሰው ቸል አለውና ጕዞውን ቀጠለ።"

ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣አንድ ሌዋዊ መጣ።( ሌዋውያን በቤተ መቅደስ ካህናቱን የሚረዱ የአይሁድ ነገድ ነበሩ።) ሌዋዊውም ደግሞ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ተሻገረና የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው በቸልታ አለፈው።"

በዚያ መንገድ የወረደው የሚቀጥለው ሰው ሳምራዊ ነበር።(ሳምራውያን የሌሎች አገሮች ሰዎችን ያገቡ የአይሁድ ዝርያዎች ነበሩ።ሳምራውያንና አይሁዳውያን እርስ በርስ ይጠላሉ ነበር።) ነገር ግን ሳምራዊው አይሁዳዊውን ባየ ጊዜ በጣም አድርጎ ራራለት። ስለዚህ ተንከባከበውና ቊስሉን አሰረለት።"

“ከዚያ በኋላ ሳምራዊው ሰውዬውን አንሥቶ በራሱ አህያ ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደሪያ ወሰደው ተንከባከበውም።”

“በማግሥቱም ሳምራዊው ጕዞውን መቀጠል አስፈለገው። ለእንግዶች ማረፊያው ባለቤት ጥቂት ገንዘብ ሰጠውና፣”ተንከባከበው፣ ከዚህ ሌላ ገንዘብ የምታወጣ ከሆነ በምመለስበት ጊዜ እከፍልሃለሁ አለው።"

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሕግ ዐዋቂውን፣ “ምን ታስባለህ? ለተዘረፈውና ለተደበደበው ሰው ባልንጀራው ከሦስቱ ሰዎች የትኛው ነበር?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ምሕረት ያደረገለት ነበር” ብሎ መለሰለት። ኢየሱስ፣ “አንተም ሄደህ እንደዚሁ አድርግ” ብሎ ነገረው።

Información relacionada

Palabras de Vida - GRN tiene mensajes audios en miles de idiomas que contienen mensajes basados en la Biblia acerca de la salvación y la vida cristiana.

Descargas gratis - Aquí puede encontrar los guiones principales de GRN en varios idiomas y también imágenes y otros materiales relacionados. Todos están disponibles para descargar.

Librería de audio de GRN - Material evangelistico y de enseñanza adecuado a las necesidades y a la cultura en variedad de stilos y formatos

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?