unfoldingWord 02 - ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ

unfoldingWord 02 - ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ

Esquema: Genesis 3

Número de guión: 1202

Idioma: Amharic

Tema: Sin and Satan (Sin, disobedience, Punishment for guilt)

Audiencia: General

Tipo: Bible Stories & Teac

Propósito: Evangelism; Teaching

Citación Biblica: Paraphrase

Estado: Approved

Los guiones son pautas básicas para la traducción y grabación a otros idiomas. Deben adaptarse según sea necesario para que sean comprendidas y relevantes para cada cultura e idioma diferentes. Algunos términos y conceptos utilizados pueden necesitar más explicación o incluso ser reemplazados o omitidos por completo.

Guión de texto

አዳምና ሚስቱ እግዚአብሔር በሠራላቸው የአትክልት ስፍራ ሲኖሩ በጣም ደስተኞች ነበሩ። ሁለቱም ራቁታቸውን ነበሩ ይሁን እንጂ ራቁታቸውን መሆናቸው እንዲተፋፈሩ አላደረጋቸውም፤ ምክንያቱም ኃጢአት በዓለም አልነበረም። እነርሱም በአትክልቱ ስፍራ እየተመላለሱ ከእግዚአብሔር ጋር ይነጋገሩ ነበር።

ነገር ግን ተንኮለኛ እባብ በአትክልቱ ውስጥ ነበር። ሴትየዋንም ጠየቃት “እግዚአብሔር በእርግጥ በአትክልቱ ውስጥ ካለው ከማንኛውም ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ ብሎችኋልን?” አላት።

ሴቲቱም፣ “እግዚአብሔር ክፉንና መልካሙን ከሚያሳውቀው የእውቀት ዛፍ በስተቀር ከማንኛውም የዛፍ ፍሬ መብላት እንደምንችል ተናግሮናል። ነገር ግን ያንን ፍሬ ብትበሉ ወይም ብትነኩት እንኳ ትሞታላችሁ” አለን።

እባቡም ለሴቲቱ መልሶ፣ “ይህ እውነት አይደለም አትሞቱም ከፍሬው በበላችሁ ጊዜ ዓይናችሁ እንደሚከፈትና መልካምና ክፉን በማወቅ እንደ እግዚአብሔርእንደምትሆኑ እግዚአብሔርስለሚያውቅ ነው አትብሉት ያላችሁ” አለ።

ሴቲቱ የዛፉ ፍሬ ለመብል መልካም፣ ለዓይን የሚያስደስትና ጥበብንም ለማግኘት የሚያጓጓ እንደ ሆነ ባየች ጊዜ ከፍሬው ወስዳ በላች። ከእርሷም ጋር ለነበረው ለባሏም ሰጠችው። እርሱም ከዛፉ ፍሬ በላ።

ወዲያውም የሁለቱም ዐይኖች ተከፈቱ። ራቁታቸውን መሆናቸውንም ተገነዘቡ፤ ቅጠልም እንደ ልብስ ሰፍተው ገላቸውን ለመሸፈን ሞከሩ።

ሰውዬውና ሚስቱም የእግዚአብሔር ድምፅ በአትክልቱ መካከል ሲመላለስ ሰምተው ሁሉም ከእግዚአብሔር ፊት ተሸሸጉ። እግዚአብሔርም አዳምን ጠርቶ “የት ነህ?” አለው። አዳምም “በአትክልቱ ስፍራ ስትመላለስ ሰማሁ ራቁቴን ስለ ሆንኩ ፈራሁ ተሸሸግሁም” ብሎ መለሰ።

እግዚአብሔርም “ራቁትህን መሆንህን ማን ነገረህ? ከርሱ እንዳትበላ ብዬ ካዘዝሁህ ዛፍ በላህን?” አለው። አዳምም፣ “ይህች ከእኔ ጋር እንድትኖር የሰጠኸኝ ሴት እርሷ ከዛፉ ፍሬ ሰጠችኝና በላሁ” አለው። እግዚአብሔር ሴቲቱንም ይህ ያደረግሽው ምንድን ነው?" አላት። እርሷም፣ “እባብ አሳሳተኝና በላሁ” አለች።

እግዚአብሔር እባቡን እንዲህ አለው፤ “የተረገምህ ነህ፣ በደረትህ ትሳባለህ አፈርም ትበላለህ አንተና ሴቲቱ ጥለኞች ትሆናላችሁ የአንተ ልጆችና የእርሷም ልጆች እንዲሁ ጥለኞች ይሆናሉ የሴቲቱ ዘር ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ተረከዙን ታቆስላለህ።”

እግዚአብሔር ሴቲቱንም አላት “በምጥ ጊዜ ጭንቅሽን አበዛለሁ፣ ፍላጎትሽ ወደ ባልሽ ይሆናል እርሱም የበላይሽ ይሆናል።”

እግዚአብሔርም አዳምን እንዲህ አለው። “የሚስትህን ቃል ሰምተህ አትብላ ብዬ ካዘዝሁህ ዛፍ ፍሬ በልተሃልና ምድር ካንተ የተነሣ ተረግማለች። በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ምግብህን ጥረህ ግረህ ከእርሷ ታገኛለህ። ከዚያም ትሞታለህ አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ።” አዳምም ሚስቱን የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ሔዋን ብሎ ጠራት ትርጓሜውም ሕይወት ሰጪ ማለት ነው፤ እግዚአብሔርም ከእንስሳ ቆዳ አዘጋጅቶ አዳምንና ሔዋንን አለበሳቸው።

እግዚአብሔርም ሰው መልካምንና ክፉን ለይቶ በማወቅ ረገድ አሁን ከእኛ እንደ አንዱ ሆኗል አሁን ደግሞ እጁን ዘርግቶ ከሕይወት ዛፍ ፍሬ ቀጥፎ እንዳይበላና ለዘላለምም እንዳይኖር አዳምና ሔዋንን ከውቡ የአትክልት ስፍራ አስወጣቸው። ከዚያም ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውን መንገድ ለመጠበቅና ማንም ከዚህ የሕይወት ዛፍ ቀጥፎ እንዳይበላ ኃይለኞች መላእክትን በአትክልቱ ስፍራ አኖረ።

Información relacionada

Palabras de Vida - GRN tiene mensajes audios en miles de idiomas que contienen mensajes basados en la Biblia acerca de la salvación y la vida cristiana.

Descargas gratis - Aquí puede encontrar los guiones principales de GRN en varios idiomas y también imágenes y otros materiales relacionados. Todos están disponibles para descargar.

Librería de audio de GRN - Material evangelistico y de enseñanza adecuado a las necesidades y a la cultura en variedad de stilos y formatos

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?