unfoldingWord 50 - ኢየሱስ ይመለሳል

unfoldingWord 50 - ኢየሱስ ይመለሳል

Outline: Matthew 13:24-42; 22:13; 24:14; 28:18; John 4:35; 15:20; 16:33; 1 Thessalonians 4:13-5:11; James 1:12; Revelation 2:10; 20:10; 21-22

Script Number: 1250

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

ለ2,000 ዓመታት ያህል በዓለም ዙሪያ ያሉ ብዙ ሰዎች ስለ መሲሑ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች እየሰሙ ቈይተዋል። ቤተ ክርስቲያን እያደገች ኖራለች። ኢየሱስ በዓም ፍጻሜ እንደሚመለስ ተስፋ ሰጥቶአል። እርሱ ገና ባይመለስም እንኳ፣ ተስፋውን ይጠብቃል።

የኢየሱስን መመለስ እየተጠባበቅን እያለን፣ እግዚአብሔር ቅዱስ በሆነና እርሱን በሚያስከብረው መንገድ እንድንኖር ይፈልጋል። ደግሞም ስለ መንግሥቱ ለሌሎች እንድንናገር ይፈልጋል። ኢየሱስ በምድር ላይ ይኖር በነበረበት ጊዜ፣ “ደቀ መዛሙርቴ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት የሚናገረውን የምሥራች በዓለም በሁሉም ስፍራ ላሉ ሰዎች ይሰብካሉ፣ በዚያን ጊዜ መጨረሻው ይመጣል” አለ።

ብዙ የሕዝብ ወገኖች አሁንም ስለ ኢየሱስ አልሰሙም። ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት፣ የምሥራቹን ከቶ ላልሰሙት ሰዎች እንዲያውጁ ለክርስቲያኖች ነገራቸው። “ሂዱና የሕዝብ ወገኖችን ሁሉ ደቀ መዛሙርት አድርጉአቸው!” “መከሩም ደርሶአል!” አለ።

ደግሞም ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “አገልጋይ ከጌታው አይበልጥም። ልክ የዚህ ዓለም ባለ ሥልጣናት እኔን እንደ ጠሉኝ፣ በእኔ ምክንያት ያሠቃዩአችሁና ይገድሉአችኋል። ምንም እንኳ በዚህ ዓለም መከራ ብትቀበሉም፣ አይዞአችሁ ምክንያቱም እኔ ይህን ዓለም የሚገዛውን ሰይጣንን አሸንፌዋለሁ። እናንተ በእኔ አምናችሁ እስከ መጨረሻ ብትጸኑ፣ በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር ያድናችኋል!”

ኢየሱስ የዓለም ፍጻሜ በሚሆንበት ጊዜ፣ በሰዎች ላይ የሚደርሰውን ነገር ለማብራራት ለደቀ መዛሙርቱ አንድ ታሪክ ነገራቸው። አንድ ሰው በእርሻው መልካም ዘርን ዘራ። ተኝቶ እያለ ጠላቱ መጣና በስንዴው ላይ የአረም ዘር ዘራበትና ሄደ።"

“የተዘራው ስንዴ በበቀለ ጊዜ፣ የሰውዬው አገልጋዮች፣ ‘ጌታው፣ በዚያ እርሻ መልካም ዘር ዘርተህ ነበር። ታዲያ በውስጡ ለምንድን ነው አረም ያለበት?’ ብለው ጠየቁት፣ጌታውም፣ ‘የዘራው ጠላት መሆን አለበት’” ብሎ መለሰላቸው።

“አገልጋዮቹ ለጌታቸው፣ ‘አረሙን እንንቀለውን?’ ብለው መለሱለት። ጌታቸው እንዲህ አለ፣ ‘አይደለም። ይህንን ብታደርጉ ስንዴውንም ትነቅሉታላችሁ። እስከ መከር ድረስ ቆዩና አረሙን ሰብስባችሁ አቃጥሉት፣ ስንዴውን ግን በጎተራዬ አከማቹት።’”

ደቀ መዛሙርቱ የታሪኩ ትርጕም አልገባቸውም፣ ስለዚህ እንዲያብራራላቸው ኢየሱስን ጠየቁት። ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “መልካሙን ዘር የዘራው ሰው መሲሑን ይወክላል። እርሻው ዓለምን ይወክላል። መልካሙ ዘር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሰዎች ይወክላል።”

“አረሙ ከክፉው ወገን የሆኑ ሰዎችን ይወክላል። አረሙን የዘራው ጠላት ዲያብሎስን ይወክላል። መከሩ የዓለምን ፍጻሜ ይወክላል፣ አጫጆቹም የእግዚአብሔርን መላእክት ይወክላሉ።

“በዓለም ፍጻሜ፣ መላእክት የዲያብሎስ ወገኖች የሆኑ ሰዎችን ሁሉ በአንድ ላይ ይሰበስቡና ወደሚንቀለቀል እሳት ይጥሉአቸዋል፣ በዚያም ይጮኻሉ አስከፊ በሆነ ሥቃይም ጥርሶቻቸውን ያፋጫሉ። በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ያበራሉ።”

ደግሞም ኢየሱስ ልክ ከዓለም ፍጻሜ በፊት ወደ ምድር እንደሚመለስ ተናገረ። በሄደበት አኳኋን ተመልሶ ይመጣል፣ ይኸውም፣ አካላዊ ሰውነት ይኖረዋል፣ በሰማይ ደመናም ይመጣል። ኢየሱስ በሚመለስበት ጊዜ እያንዳንዱ የሞተ ክርስቲያን ከሙታን ይነሣና በሰማይ ይገናኘዋል።

በዚያን ጊዜ ገና በሕይወት ያሉ ክርስቲያኖች ወደ ሰማይ ይነጠቁና ከሙታን ከተነሡ ሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ይቀላቀላሉ። በዚያ ሁላቸውም ከኢየሱስ ጋር ይሆናሉ። ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ከሕዝቡ ጋር ፍጹም በሆነ ሰላምና አንድነት ለዘላለም ይኖራል።

ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ ዘውድ ለመስጠት ተስፋ ሰጥቶአል። እነርሱ ፍጹም በሆነ ሰላም ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም ይኖራሉ ይነግሣሉም።

ነገር ግን እግዚአብሔር በኢየሱስ በማያምኑ ሁሉ ላይ ይፈርዳል። ለዘላለም ወደሚያለቅሱበትና በሥቃይ ጥርሶቻቸውን ወደሚያፏጩበት ወደ ሲኦል ይጥላቸዋል። ከቶ የማይጠፋ እሳት ባለማቋረጥ ያቃጥላቸዋል፣ ትሎችም እነርሱን መብላታቸውን በጭራሽ አያቋርጡም።

ኢየሱስ በሚመለሰበት ጊዜ፣ ሰይጣንና መንግሥቱን ሙሉ በሙሉ ያጠፋቸዋል። ሰይጣንን ለእግዚአብሔር ከመታዘዝ ይልቅ እርሱን ለመከተል ከመረጡት ሁሉ ጋር ለዘላለም ወደሚቃጠሉበት ወደ ሲኦል ይጥለዋል።

አዳምና ሔዋን ለእግዚአብሔር ስላልታዘዙና ኃጢአትን ወደዚህ ዓለም ስላመጡ፣ እግዚአብሔር ዓለምን ረገማት ሊያጠፋትም ወሰነ። ነገር ግን አንድ ቀን እግዚአብሔር ፍጹም የሚሆን ዐዲስ ሰማይና ዐዲስ ምድር ይፈጥራል።

ኢየሱስና ሕዝቡ በዐዲሲቱ ምድር ይኖራሉ፣ ባለው ሁሉ ነገር ላይ ለዘላለም ይነግሣሉ። እርሱ እንባን ሁሉ ያብሳል፣ ከእንግዲህ ሥቃይ፣ ሐዘን፣ ልቅሶ፣ ክፋት፣ ሕመም፣ ወይም ሞት አይኖርም። ኢየሱስ መንግሥቱን በሰላምና በፍትሕ ይገዛል፣ ለዘላለምም ከሕዝቡ ጋር ይሆናል።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons