unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ

unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ

Outline: Matthew 4:12-25; Mark 1-3; Luke 4

Script Number: 1226

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

ኢየሱስ የሰይጣንን ፈተና ካሸፈነ በኋላ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይኖርበት ወደ ነበረው ወደገሊላ አውራጃ ተመለሰ። ኢየሱስ ከቦታ ወደ ቦታ እየሄደ አስተማረ።ሁሉም ሰው ስለ እርሱ መልካም ይናገሩ ነበር።

ኢየሱስ በልጅነቱ ወደ ኖረበት ወደ ናዝሬትከተማ ተመለሰ። በሰንበት ወደ አምልኮ ቦታ ሄደ።ያነብ ዘንድ የነቢዩን የኢሳይያስን ጥቅልልጽሑፍ ሰጡት። ኢየሱስ ጥቅልል ጽሑፉን ከፍቶ በከፊል ለሕዝቡ አነበበላቸው።

ኢየሱስ፣ “ለድሆች የምሥራችን፣ ለተማረኩት ነጻትን፣ ለዕውሮች ማየትን፣ ለታሰሩትም መፈታትን እሰብክዘንድ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰጥቶኛል።ይህች የተወደደችውየጌታ ዓመት ነች” ብሎ አነበበ።

ከዚያም ኢየሱስ ተቀመጠ። ሁላቸውም በቅርበት ተመለከቱት። ልክ አሁን ያነበበው የእግዚአብሔር ቃል ምንባብ መሲሑን ያመለክት ነበር። ኢየሱስ፣“ይህ ያነበብኩላችሁ ቃል ልክአሁን እየተፈጸመ ነው” አለ።ሕዝቡ ሁሉ ተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን?” አሉ።

ከዚያም ኢየሱስ፣“ነቢይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር እውነትነው፣ በነቢዩ ኤልያስ ዘመን፣ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ።ነገር ግን ለሦስትዓመት ተኩል ዝናብ ባልዘነበ ጊዜ እግዚአብሔር ኤልያስን በተለየአገር እንጂ በእስራኤልያለች መበለትን እንዲረዳ አልላከውም።”

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መናገሩን ቀጠለ፣ “በነቢዩ ኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል የቆዳ ሕመም የያዛቸው ብዙ ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን ኤልሳዕ አንዳቸውንም አልፈወሰም። የእስራኤል ጠላቶች አዛዥ የነበረውን የንዕማንን ቆዳ በሽታ ብቻ ፈወሰ።” ኢየሱስን ይሰሙ የነበሩት ሕዝብ አይሁዳውያን ነበሩ። ስለዚህ ይህን ሲናገር በሰሙት ጊዜ ተናደዱበት።

የናዝሬት ሕዝብ ኢየሱስን ከአምልኮው ቦታ ጐተቱትና ወርውረው ሊገድሉት ወደ ተራራውአፋፍ ወሰዱት።ነገር ግን ኢየሱስ በሕዝቡ መካከል ተራመደና ወደ ናዝሬትከተማ ሄደ።

ከዚያም ኢየሱስ በገሊላ አውራጃ ሁሉ ተዘዋወረ፣ ብዙ ሕዝብም ወደ እርሱ መጡ። ማየት፣ መራመድ፣ መስማት፣ ወይም መናገር የማይችሉትን ጨምሮ ብዙ የታመሙ ወይም የአካል ጕዳተኞች የሆኑ ሰዎችን አመጡ።

አጋንንት የነበሩባቸው ብዙ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ። በኢየሱስ ትእዛዝ አጋንንቱ ከሰዎቹ ወጡ፣ ብዙ ጊዜም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” ብለው ጮኹ። ሕዝቡ ተደነቁና እግዚአብሔርን አመለኩ።

ከዚያም ኢየሱስደቀ መዛሙርቱ ተብለው የተጠሩትን ዐሥራ ሁለት ሰዎች መረጠ። ሐዋርያቱ ከኢየሱስ ጋር ተጓዙና ከእርሱ ተማሩ።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons