unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

Outline: Matthew 3; Mark 1; Luke 3; John 1:15-37

Script Number: 1224

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ዮሐንስ አደገና ነቢይ ሆነ። በምድረ በዳ ኖረ፣ የበረሐ ማርና አንበጣ ተመገበ፣ ከግመል ፀጉር የተሠራ ልብስም ለበሰ።

ብዙ ሕዝብ ዮሐንስን ለመስማት ወደ ምድረ በዳ መጡ። እርሱም፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” በማለት ሰበከላቸው።

ሕዝቡ የዮሐንስን መልእክት በሰሙ ጊዜ፣ አብዛኞቻቸው ኃጢአታቸውን ተናዘዙ፣ ዮሐንስም አጠመቃቸው። ብዙ የሃይማኖት መሪዎች ደግሞ በዮሐንስ ሊጠመቁ መጡ፣ ነገር ግን ንስሐ አልገቡም ወይም ኃጢአታቸውን አልተናዘዙም።

ዮሐንስ ለሃይማኖት መሪዎቹ እንዲህ አላቸው፣ “እናንተ መርዛማ እባቦች! ንስሐ ግቡና ድርጊታችሁን ለውጡ። መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጥና ወደ እሳት ይጣላል።” ዮሐንስ ነቢያት “እነሆ፣ መንገድህን የሚያዘጋጅ መልእክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ።” በማለት የተናገሩትን ፈጽመ።

አንዳንድ አይሁዶች መሲሕ ስለ መሆኑ ዮሐንስን ጠየቁት። ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መለሰ፣ “እኔ መሲሑ አይደለሁም፣ ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣ አንድ ሰው አለ። የጫማውን ማሰሪያ ልፈታ እንኳ የማይገባኝ በጣም ታላቅ ነው።”

በቀጣዩ ቀን፣ ኢየሱስ በዮሐንስ ለመጠመቅ መጣ። ዮሐንስ ባየው ጊዜ፣ “ተመልከቱ! እነሆ፣ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ” አለ።

ዮሐንስ ኢየሱስን፣ “እኔ አንተን ለማጥመቅ ተገቢ ሰው አይደለሁም። በዚህ ፈንታ አንተ እኔን ማጥመቅ አለብህ እንጂ” አለው። ኢየሱስ ግን፣ “መደረግ ያለበት ትክክለኛ ነገር ነውና አንተ እኔን ማጥመቅ ይገባሃል” አለ። ስለዚህ ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት ባይሠራም እንኳ ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀው።

ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ከውኃው እንደ ወጣ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ በርግብ አምሳል ታየና ወርዶ በእርሱ ላይ ዐረፈ። በዚሁ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ፣ “አንተ እኔ የምወድህ ልጄ ነህ፣ በአንተም በጣም ደስ ብሎኛል” ብሎ ተናገረ።

እግዚአብሔር ለዮሐንስ፣ “መንፈስ ቅዱስ ይወርድና አንተ በምታጠምቀው ሰው ላይ ያርፋል። ሰውዬው የእግዚአብሔር ልጅ ነው” ብሎ ተናግሮት ነበር። አንድ አምላክ ብቻ አለ። ነገር ግን ዮሐንስ ኢየሱስን ባጠመቀው ጊዜ፣ እግዚአብሔር አብ ሲናገር ሰማ፣ እግዚአብሔር ወልድን ዐየ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው፣ እንዲሁም መንፈስ ቅዱስን ዐየ።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons