unfoldingWord 12 - የእስራኤላውያን ከግብፅ መውጣት

unfoldingWord 12 - የእስራኤላውያን ከግብፅ መውጣት

Outline: Exodus 12:33-15:21

Script Number: 1212

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

እስራኤላውያን ከግብፅ በመውጣታቸው በጣም ደስ አላቸው። ከእንግዲህ ባሪያዎች አይደሉም፣ ወደ ተስፋዪቱ ምድርም በመጓዝ ላይ ነበሩ! ግብፃውያን ለእስራኤላውያን ወርቅና ብር ሌሎችም የከበሩ ነገሮች ሳይቀሩ የጠየቁትን ማንኛውንም ነገር ሰጡአቸውና ከግብፅ ሲወጡ ከሌሎች ብሔሮች የሆኑ አንዳንድ ሰዎች በእግዚአብሔር አምነው ከእስራኤላውያን ጋር ሄዱ።

እግዚአብሔር በፊታቸው በሚሄድ ቀን ረጅም በሆነ የደመና ዓምድ፣ ማታም ረጅም በሆነ የእሳት ዓምድ መራቸው። እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከእነርሱ ጋር ነበርና ሲጓዙ መራቸው። ማድረግ ያለባቸው ነገር ቢኖር እርሱን መከተል ብቻ ነበር።

ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ፈርዖንና ሕዝቡ ዐሳባቸውን ለወጡና እስራኤላውያን እንደ ገና የእነርሱ ባሪያዎች እንዲሆኑ ፈለጉ። እግዚአብሔር ብቸኛው እውነተኛ አምላክ መሆኑን ሕዝቡ እንዲያዩ፣ እንዲሁም እርሱ፣ ያሕዌ፣ ከፈርዖንና ከአማልክቱ የበለጠ ኃያል እንደ ሆነ ይረዱ ዘንድ ፈርዖንን ዐሳበ ግትር አደረገው።

ስለዚህ ፈርዖንና ጦር ሠራዊቱ እንደ ገና ባሪያዎቻቸው ሊያደርጉአቸው እስራኤላውያንን አሳደዱአቸው። እስራኤላውያን የግብፅ ጦር ሠራዊት ሲመጣ ባዩ ጊዜ፣ በፈርዖን ጦር ሠራዊትና በቀይ ባሕር መካከል እንደ ተጠመዱ ዐወቁ። በጣም ፈርተው ስለ ነበር፣ “ከግብፅ ለምን ወጣን? መሞታችን ነው!” ብለው ጮኹ።

ሙሴ እስራኤላውያንን፣ “አትፍሩ! ዛሬ እግዚአብሔር ይዋጋላችሁና ያድናችኋል” ብሎ ነገራቸው። ከዚያም እግዚአብሔር፣ “ወደ ቀይ ባሕር እንዲንቀሳቀሱ ለሕዝቡ ንገራቸው” ብሎ ለሙሴ ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር ግብፃውያን እስራኤላውያንን ማየት እንዳይችሉ የደመናውን ዓምድ በእስራኤላውያንና በግብፃውያን መካከል አደረገው።

እግዚአብሔር ለሙሴ በባሕሩ ላይ እጁን እንዲዘረጋና ውሃውን እንዲከፍለው ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር በባሕሩ መተላለፊያ መንገድ ይኖር ዘንድ ውሃውን ነፋስ ወደ ግራና ወደ ቀኝ እንዲያንቀሳቅሰው አደረገ።

እግዚአብሔር ለሙሴ በባሕሩ ላይ እጁን እንዲዘረጋና ውሃውን እንዲከፍለው ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር በባሕሩ መተላለፊያ መንገድ ይኖር ዘንድ ውሃውን ነፋስ ወደ ግራና ወደ ቀኝ እንዲያንቀሳቅሰው አደረገ።

እስራኤላውያን ውሃው በግራና በቀኛቸው ግድግዳ ሆኖላቸው በባሕሩ በደረቅ መሬት ላይ ተጓዙ።

ከዚያም እግዚአብሔር ግብፃውያኑ እስራኤላውያን ማምለጣቸውን ያዩ ዘንድ ደመናውን ከመንገዱ ወደ ላይ አንቀሳቀሰው። ግብፃውያን ከኋላቸው ሆነው ሊያሳድዱአቸው ወሰኑ።

ስለዚህ በባሕሩ መንገድ እስራኤላውያንን ተከተሉአቸው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ግብፃውያን እንዲጨነቁና ሰረገሎቻቸውም እንዲታሰሩ አደረገ። “ሽሹ! እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እየተዋጋላቸው ነው!” ብለው ጮኹ።

እስራኤላውያን ባሕሩን በደኅና ከተሻገሩ በኋላ፣ እግዚአብሔር እንደ ገና እጁን እንዲዘረጋ ለሙሴ ነገረው። እርሱም በታዘዘ ጊዜ፣ ውሃው በግብፃውያን ሠራዊት ላይ ተመለሰና እንደ መጀመሪያው ሆነ። መላው የግብፃውያን ጦር ሠራዊት ሰጠመ።

እስራኤላውያን ግብፃውያን እንደ ሞቱ ባዩ ጊዜ በእግዚአብሔር አመኑ ሙሴም የእግዚአብሔር ነቢይ መሆኑን አመኑ።

ደግሞም እስራኤላውያን እግዚአብሔር ከሞትና ከባርነት ስለ አዳናቸው በብዙ ደስታ ደስ አላቸው! አሁን እግዚአብሔርን ለማገልገል ነጻ ሆኑ። እስራኤላውያን እርሱ ከግብፃውያን ጦር ሠራዊት ስለ አዳናቸው ዐዲሱን ነጻነታቸውን ለማክበርና እግዚአብሔርን ለማመስገን ብዙ መዝሙሮችን ዘመሩ።

እንዴት እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ድልን እንደ ሰጣቸውና ባሪያዎች ከመሆን እንዳዳናቸው ያስታውሱ ዘንድ በያመቱ ፋሲካን እንዲያከብሩ እስራኤላውያንን አዘዛቸው። ፍጹም የሆነ ጠቦት አርደው ካልቦካ ቂጣ ጋር በመብላት ተደሰቱ።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons