unfoldingWord 02 - ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ

unfoldingWord 02 - ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ

Outline: Genesis 3

Script Number: 1202

Language: Amharic

Theme: Sin and Satan (Sin, disobedience, Punishment for guilt)

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

አዳምና ሚስቱ እግዚአብሔር በሠራላቸው የአትክልት ስፍራ ሲኖሩ በጣም ደስተኞች ነበሩ። ሁለቱም ራቁታቸውን ነበሩ ይሁን እንጂ ራቁታቸውን መሆናቸው እንዲተፋፈሩ አላደረጋቸውም፤ ምክንያቱም ኃጢአት በዓለም አልነበረም። እነርሱም በአትክልቱ ስፍራ እየተመላለሱ ከእግዚአብሔር ጋር ይነጋገሩ ነበር።

ነገር ግን ተንኮለኛ እባብ በአትክልቱ ውስጥ ነበር። ሴትየዋንም ጠየቃት “እግዚአብሔር በእርግጥ በአትክልቱ ውስጥ ካለው ከማንኛውም ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ ብሎችኋልን?” አላት።

ሴቲቱም፣ “እግዚአብሔር ክፉንና መልካሙን ከሚያሳውቀው የእውቀት ዛፍ በስተቀር ከማንኛውም የዛፍ ፍሬ መብላት እንደምንችል ተናግሮናል። ነገር ግን ያንን ፍሬ ብትበሉ ወይም ብትነኩት እንኳ ትሞታላችሁ” አለን።

እባቡም ለሴቲቱ መልሶ፣ “ይህ እውነት አይደለም አትሞቱም ከፍሬው በበላችሁ ጊዜ ዓይናችሁ እንደሚከፈትና መልካምና ክፉን በማወቅ እንደ እግዚአብሔርእንደምትሆኑ እግዚአብሔርስለሚያውቅ ነው አትብሉት ያላችሁ” አለ።

ሴቲቱ የዛፉ ፍሬ ለመብል መልካም፣ ለዓይን የሚያስደስትና ጥበብንም ለማግኘት የሚያጓጓ እንደ ሆነ ባየች ጊዜ ከፍሬው ወስዳ በላች። ከእርሷም ጋር ለነበረው ለባሏም ሰጠችው። እርሱም ከዛፉ ፍሬ በላ።

ወዲያውም የሁለቱም ዐይኖች ተከፈቱ። ራቁታቸውን መሆናቸውንም ተገነዘቡ፤ ቅጠልም እንደ ልብስ ሰፍተው ገላቸውን ለመሸፈን ሞከሩ።

ሰውዬውና ሚስቱም የእግዚአብሔር ድምፅ በአትክልቱ መካከል ሲመላለስ ሰምተው ሁሉም ከእግዚአብሔር ፊት ተሸሸጉ። እግዚአብሔርም አዳምን ጠርቶ “የት ነህ?” አለው። አዳምም “በአትክልቱ ስፍራ ስትመላለስ ሰማሁ ራቁቴን ስለ ሆንኩ ፈራሁ ተሸሸግሁም” ብሎ መለሰ።

እግዚአብሔርም “ራቁትህን መሆንህን ማን ነገረህ? ከርሱ እንዳትበላ ብዬ ካዘዝሁህ ዛፍ በላህን?” አለው። አዳምም፣ “ይህች ከእኔ ጋር እንድትኖር የሰጠኸኝ ሴት እርሷ ከዛፉ ፍሬ ሰጠችኝና በላሁ” አለው። እግዚአብሔር ሴቲቱንም ይህ ያደረግሽው ምንድን ነው?" አላት። እርሷም፣ “እባብ አሳሳተኝና በላሁ” አለች።

እግዚአብሔር እባቡን እንዲህ አለው፤ “የተረገምህ ነህ፣ በደረትህ ትሳባለህ አፈርም ትበላለህ አንተና ሴቲቱ ጥለኞች ትሆናላችሁ የአንተ ልጆችና የእርሷም ልጆች እንዲሁ ጥለኞች ይሆናሉ የሴቲቱ ዘር ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ተረከዙን ታቆስላለህ።”

እግዚአብሔር ሴቲቱንም አላት “በምጥ ጊዜ ጭንቅሽን አበዛለሁ፣ ፍላጎትሽ ወደ ባልሽ ይሆናል እርሱም የበላይሽ ይሆናል።”

እግዚአብሔርም አዳምን እንዲህ አለው። “የሚስትህን ቃል ሰምተህ አትብላ ብዬ ካዘዝሁህ ዛፍ ፍሬ በልተሃልና ምድር ካንተ የተነሣ ተረግማለች። በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ምግብህን ጥረህ ግረህ ከእርሷ ታገኛለህ። ከዚያም ትሞታለህ አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ።” አዳምም ሚስቱን የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ሔዋን ብሎ ጠራት ትርጓሜውም ሕይወት ሰጪ ማለት ነው፤ እግዚአብሔርም ከእንስሳ ቆዳ አዘጋጅቶ አዳምንና ሔዋንን አለበሳቸው።

እግዚአብሔርም ሰው መልካምንና ክፉን ለይቶ በማወቅ ረገድ አሁን ከእኛ እንደ አንዱ ሆኗል አሁን ደግሞ እጁን ዘርግቶ ከሕይወት ዛፍ ፍሬ ቀጥፎ እንዳይበላና ለዘላለምም እንዳይኖር አዳምና ሔዋንን ከውቡ የአትክልት ስፍራ አስወጣቸው። ከዚያም ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውን መንገድ ለመጠበቅና ማንም ከዚህ የሕይወት ዛፍ ቀጥፎ እንዳይበላ ኃይለኞች መላእክትን በአትክልቱ ስፍራ አኖረ።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons