unfoldingWord 21 - እግዚአብሔር መሲሑን ተስፋ ሰጠ

unfoldingWord 21 - እግዚአብሔር መሲሑን ተስፋ ሰጠ

Script Number: 1221

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

ገና ከመጀመሪያው፣ እግዚአብሔር መሲሑንለመላክ ዐቀደ። የመጀመሪያው የመሲሑ ተስፋ ወደ አዳምና ሔዋን መጣ። እግዚአብሔርየእባቡን ራስ የሚቀጠቅጥ የሔዋን ዘር እንደሚወለድ ተስፋ ሰጠ። ሔዋንን ያታለለው እባብ ሰይጣን ነበር። ተስፋው መሲሑ ሰይጣንን ፍጹም ያሸንፈዋል ማለት ነው።

በእርሱ በኩል የዓለም ሕዝብ ወገኖች በሙሉ በረከት እንደሚቀበሉ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ ሰጠው። ይህ በረከት ወደ ፊት መሲሑ ሲመጣ ይፈጸማል። እርሱ በዓለም ካሉ ከሁሉም የሕዝብ ወገኖች የሆኑ ሕዝቦች እንዲድኑ ያደርጋል።

ወደ ፊት እንደ ሙሴ ያለ ሌላ ነቢይ እንደሚያስነሣ እግዚአብሔር ለሙሴ ተስፋ ሰጠው። ይህ ቆይቶ ስለሚመጣው መሲሕ የተሰጠ ሌላ ተስፋ ነበር።

ከዝርያዎቹ አንዱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ንጉሥ ሆኖ ለዘላለም እንደሚገዛ እግዚአብሔር ለንጉሥ ዳዊት ተስፋ ሰጠው። ይህም መሲሑ ከዳዊት ዝርያዎች አንዱ ይሆናል ማለት ነበር።

እግዚአብሔር ዐዲስ ቃል ኪዳን እንደሚያደርግ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል ተስፋ ሰጠ፣ ይህ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር በሲና ከእስራኤል ጋር እንዳደረገው ቃል ኪዳን ግን አይደለም። በዐዲሱ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር ሕጉን በሕዝቡ ልብ ይጽፋል፣ ሕዝቡ በግል እግዚአብሔርን ያውቁታል፣ ሕዝቡ ይሆናሉ፣ እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ይቅር ይላል። መሲሑ ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።

ደግሞም የእግዚአብሔር ነቢያት መሲሑ ነቢይ፣ ካህን እንዲሁም ንጉሥ ይሆናል አሉ። ነቢይ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ከዚያም የእግዚአብሔርን ቃል ለሕዝቡ የሚያውጅ ሰው ነው። እግዚአብሔር ለመላክ ተስፋ የሰጠው መሲሕ ፍጹም ነቢይ ይሆናል።

እስራኤላውያን ካህናት ስለ ኃጢአታቸው በሚደርስባቸው ቅጣት ምትክ በሕዝቡ ፈንታ ለእግዚአብሔር መሥዋዕቶችን አቀረቡ። ደግሞም ካህናት ስለ ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ። መሲሑ ፍጹም መሥዋዕት አድርጎ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚያቀርብ ፍጹም ሊቀ ካህናት ይሆናል።

ንጉሥ በመንግሥቱ ላይ የሚገዛና በሕዝቡ ላይ የሚፈርድ ሰው ነው። መሲሑ በቅድማያቱ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ፍጹም ንጉሥ ይሆናል። በመላው ዓለም ላይ ለዘላለም ይገዛል፣ እንዲሁም ሁልጊዜ በቅንነት ይፈርድና ትክክለኛ ውሳኔ ይሰጣል።

የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ ሌሎች ብዙ ነገሮችን ተንብየዋል። ነቢዩ ሚልክያስ መሲሑ ከመምጣቱ በፊት ታላቅ ነቢይ እንደሚመጣ አስቀድሞ ተነበየ። መሲሑ ከአንዲት ድንግል እንደሚወለድ ነቢዩ ኢሳይያስ ተነበየ። ነቢዩ ሚክያስ መሲሑ በቤተ ልሔም ከተማ ይወለዳል አለ።

ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ በገሊላ ይኖራል፣ ልባቸው የተሰበረ ሰዎችን ያጽናናል፣ እንዲሁም ለተማረኩት ነጻነትንና ለታሰሩት መፈታትን ያውጃል። ደግሞም ነቢዩ መሲሑ የታመሙና መስማት፣ ማየት፣ መናገር፣ ወይም መራመድ የማይችሉትን ሕዝብ እንደሚፈውስ ተነበየ።

ደግሞም ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ ያለ ምክንያት እንደሚጠላና ተቃውሞ እንደሚደርስበት ተነበየ። ሌሎች ነቢያት መሲሑን የገደሉት እነዚያ በልብሶቹ ላይ ዕጣ እንደሚጣጣሉና ወዳጁ እንደሚክደው አስቀድመው ተነበዩ። ነቢዩ ዘካርያስ መሲሑን ለሚክደው ወዳጅ ሠላሳ ብር እንደሚከፍሉት ተነበየ።

ደግሞም ነቢዩ ስለ መሲሑ አሟሟት ተናገረ። ኢሳይያስ ሰዎች መሲሑን እንደሚተፉበት፣ እንደሚያፌዙበትና እንደሚመቱት ተነበየ። ምንም ስሕተት ነገር ያላደረገ ቢሆንም እንኳ ይወጉታል በታላቅ ሕመምና ሥቃይ ይሞታል።

ደግሞም ነቢያት መሲሑ ኃጢአት የሌለበት ፍጹም ይሆናል አሉ። የሌሎች ሰዎችን ኃጢአት ቅጣት ለመቀበል እርሱ ሞተ። የእርሱ መቀጣት በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ሰላምን ያመጣል። በዚህ ምክንያት መሲሑን ማድቀቅ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር።

መሲሑ እንደሚሞትና እግዚአብሔር ደግሞ ከሙታን እንደሚያስነሣው ነቢያት አስቀድመው ተነበዩ። እግዚአብሔር በመሲሑ ሞትና ትንሣኤ በኩል ኃጢአተኞችን ለማዳን ዕቅዱን ይፈጽምና ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።

እግዚአብሔር ለነቢያት ስለ መሲሑ ብዙ ነገሮችን ገለጠላቸው፣ ነገር ግን መሲሑ ከእነዚያ ነቢያት በአንዳቸውም ጊዜ አልመጣም። ከእነዚህ ትንቢቶች የመጨረሻው ከተተነበየ ከ400 ዓመታት በኋላ፣ ልክ በትክክለኛው ጊዜ፣ እግዚአብሔር መሲሑን ወደ ዓለም ይልካል።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons