unfoldingWord 04 - የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከአብርሃም ጋር

unfoldingWord 04 - የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከአብርሃም ጋር

Raamwerk: Genesis 11-15

Skripnommer: 1204

Taal: Amharic

Tema: Living as a Christian (Obedience, Leaving old way, begin new way); Sin and Satan (Judgement, Heart, soul of man)

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bybelaanhaling: Paraphrase

Status: Approved

Skrips is basiese riglyne vir vertaling en opname in ander tale. Hulle moet so nodig aangepas word dat hulle verstaanbaar en relevant is vir elke verskillende kultuur en taal. Sommige terme en konsepte wat gebruik word, het moontlik meer verduideliking nodig of selfs heeltemal vervang of weggelaat word.

Skripteks

ከጥፋት ውሃው ከብዙ ዓመታትበኋላ ሕዝቦች በዓለም ላይ እንደገና በዙ።ሁሉም አንድ አይነትቋንቋ ይናገሩ ነበር። እግዚአብሔር እንዳዘዛቸው ምድርን ከመሙላትይልቅ በአንድነት ተሰብስበውከተማ ሠሩ።

እነርሱም በጣም ትምክህተኞችና እግዚአብሔር ለተናገራቸው ነገር ያልተጠነቀቁ ነበሩ። እንዲያውም ወደ ሰማይ ሊደርሱ ረጅም ሕንጻ መገንባት ጀመሩ። እግዚአብሔርም እነዚህ ሰዎች ክፉ መሥራታቸውንና በዚህም መቀጠላቸውን አየ። ከዚህም የከፋ ኃጢአት ማድረግ ይችሉም ነበር።

ስለዚህም እግዚአብሔር ቋንቋቸውን ወደ ብዙ የተለያዩ ቋንቋዎች ለወጠና ሕዝቡን በዓለም ሁሉ በተናቸው። ሊሠሩት የጀመሩት ከተማ ስም ባቢሎን ይባላል። የስሙም ትርጓሜ የተደባለቀ ወይም ግራ የተጋባ ማለት ነው።

ከመቶ ዓመታት በኋላ እግዚአብሔር አብራም የተባለውን ሰው ተናገረው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው አገርህንና ቤተ ሰብህን ትተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ። በዚያም እባርክሃለሁ፣ ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ ስምህንም ታላቅ አደርገዋለሁ፣ የሚባርኩህን እባርካለሁ፣ የሚረግሙህንም እረግማለሁ ባንተ ምክንያትም የምድር ሰዎች ሁሉ ይባረካሉ።

አብራምም እግዚአብሔርን ታዘዘ ሚስቱን ሦራንና አገልጋዮቹን ሁሉና ንብረቱንም ሁሉ ይዞ እግዚአብሔር ወዳሳየው የከነዓን ምድር ሄደ።

አብራም ከነዓን በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር “በዙሪያህ ያለውን ሁሉ ተመልከት የምታየውን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘሮችህ ውርስ አድርጌ እሰጣችኋለሁ” አለው። አብራምም በምድር ተቀመጠ።

ከዕለታት አንድ ቀን አብራም መልከ ጼዴቅ የተባለውን ታላቁን የእግዚአብሔር ሊቀ ካህናት ተገናኘው። መልከ ጻዴቅም አብራምን ባረከው እንዲህም አለው “የሰማይና የምድር ጌታ ታላቁ እግዚአብሔር አብራምን ይባርክ” አብራምም ለመልከ ጼዴቅ ካለው ሁሉ አሥራት ሰጠው።

ብዙ ዓመታት ቢያልፉም አብራምና ሦራ አሁንም ያለ ልጅ ይኖሩ ነበር። እግዚአብሔር ለአብራም እንደ ገና ተስፋ ሰጠው ልጅ እንደሚኖረውና ዘሮቹ እንደ ሰማይ ክዋክብት እንደሚበዙ ተናገረው። አብራምም በእግዚአብሔር ተስፋ አመነ። አብራምም በእግዚአብሔር ተስፋ በማመኑ ምክንያት ጻድቅ ሆኖ ተቈጠረ።

እግዚአብሔርምከአብራም ጋር ቃልኪዳን አደረገ። ቃልኪዳን በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ ስምምነት ነው። እግዚአብሔርም አብራምን“ከገዛ አብራክህ ልጅእሰጥሃለሁ” አለው።“ለዘሮችህም የከነዓንን ምድር እሰጣለሁ።” አብራምግን በዚያን ጊዜ ያለ ልጅ ነበር።

Verwante inligting

Woorde van Lewe - GRN het oudio-evangelieboodskappe in duisende tale wat Bybelgebaseerde boodskappe bevat oor verlossing en Christelike lewe.

Gratis aflaaie - Hier vind u al die belangrikste GRN boodskap skrips in verskeie tale, plus prente en ander verwante materiaal, wat beskikbaar is om af te laai.

Die GRN Oudiobiblioteek - Evangelistiese en basiese Bybelonderrigmateriaal wat geskik is vir die behoefte en kultuur van die mense in 'n verskeidenheid style en formate.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?