unfoldingWord 03 - የጥፋት ውሃ

unfoldingWord 03 - የጥፋት ውሃ

Zusammenfassung: Genesis 6-8

Skript Nummer: 1203

Sprache: Amharic

Thema: Eternal life (Salvation); Living as a Christian (Obedience); Sin and Satan (Judgement)

Zuschauer: General

Genre: Bible Stories & Teac

Zweck: Evangelism; Teaching

Bibelzitat: Paraphrase

Status: Approved

Skripte dienen als grundlegende Richtlinie für die Übersetzung und Aufnahme in anderen Sprachen. Sie sollten, soweit erforderlich, angepasst werden, um sie für die jeweilige Kultur und Sprache verständlich und relevant zu machen. Einige der verwendeten Begriffe und Konzepte müssen unter Umständen ausführlicher erklärt oder sogar ersetzt oder ganz entfernt werden.

Skript Text

ከረጅም ጊዜ በኋላ ብዙ ሕዝቦች በዓለም ይኖሩ ነበር። እነርሱም በጣም ክፉዎችና ኃይለኞች ሆኑ። ክፋትም በጣም እየበዛ በመምጣቱ እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ በሚያጥለቀልቅ የጥፋት ውሃ አጠፋለሁ ሲል ወሰነ።

ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አገኘ። ኖኅ በዘመኑ ከነበሩት ሰዎች ሁሉይልቅ ጻድቅና ከበደል የራቀ ሰው ነበር።እግዚአብሔርም ሊልክ ስላቀደው የጥፋት ውሃለኖኅ ነገረው። ኖኅ ግዙፍ መርከብ እንዲሠራ እግዚአብሔርነገረው።

እግዚአብሔርም ለኖኅ መርከብ እንዲሠራ ነገረው። የመርከቢቱም ርዝመት 140 ሜትር ወርዷ 23 ሜትር ከፍታዋ 13.5 ሜትር ይሁን አለ። ኖኅ የሚሠራት መርከብ ከእንጨት የተሠራች ሆና ባለ ሦስት ፎቅ፤ ብዙ ክፍሎች ጣራና መስኮት ያሉአት ነበረች፤ መርከቢቱም ኖኅንና ቤተ ሰቡን፣ ሁሉንም ዓይነት የምድር ላይ እንስሳት ከጥፋት ውሃ እንድትጠብቅ ነገረው።

ኖኅም እግዚአብሔርን በመታዘዘ እግዚአብሔር እንደ ነገራቸውም ኖኅና ሦስቱ ልጆቹ መርከቢቱን ሠሩ። መርከቧ በጣም ትልቅ ነበረችና ሲሠራ ብዙ ዓመታት ፈጀ። ኖኅ ስለሚመጣው የጥፋት ውሃ ለሕዝቡ እያስጠነቀቀ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ ይነግራቸው ነበር ይሁን እንጂ አላመኑትም።

እግዚአብሔር ኖኅንና ቤተ ሰቡን በቂ ምግብ ለራሳቸውና ለእንስሳቱ እንዲያከማቹ አዘዘ ሁሉም ነገር ዝግጁ በሆነ ጊዜ ወደ መርከቢቱ ለመግባት ለኖኅ፣ ለሚስቱ፣ ለሦስቱ ወንዶች ልጆቹና ለሚስቶቻቸው ጊዜው መድረሱን ነገረው። ስምንት ሰዎችም ወደ መርከቢቱ ገቡ።

እግዚአብሔር ከጥፋት ውሃው እንዲጠበቁ የሁሉንም ተባእትና እንስት እንስሳት ወፎችን ጨምሮ ወደ ኖኅ ላከ። ለመሥዋዕት የሚያገለግሉ ሰባት ተባእትና ሰባት እንስት ከሁሉም ዓይነት እንስሳ ወደ ኖኅ መርከብ ላካቸው። ሁሉም ወደ መርከቡ እንደ ገቡ እግዚአብሔር ራሱ የመርከቡን በር ዘጋ።

ከዚያም ዝናቡ መዝነብ ጀመረ፣ ዘነበ፣ ዘነበ፣ ዘነበ ያለማቋረጥ ለ40 ቀንና ሌሊት ዘነበ፣ ከምድርም ምንጭ ይፈልቅ ነበር። በመላው ዓለም ያለው ሁሉም ነገር በውሃ ተሸፈነ፤ ረጃጅም ተራሮች እንኳ ሳይቀሩ በውሃ ተሸፈኑ።

በመርከቡ ከነበሩት ሰዎችና እንስሳት በቀር በምድር ይኖር የነበረ ነገር ሁሉ ሞተ፤ መርከቢቱም በውሃው ላይ ተንሳፍፋ በውስጧ የሚገኙትን ነፍሳት ሁሉ ከሞት አዳነች (አተረፈች)።

ዝናቡ መዝነቡን ካቆመ በኋላ መርከቢቱ ለአምስት ወራት ያህል በውሃው ላይ ተነሳፈፈች። በዚህም ጊዜ ውሃው መቀነስ ጀመረ። ከዕለታት አንድ ቀን መርከቢቱ በተራራው አናት ላይ አረፈች፤ ይሁን እንጂ ዓለም አሁንም በውሃ ተሸፍና ነበር። ከሦስት ወራት በኋላ የተራራ ጫፎች መታየት ጀመሩ።

ከአርባ ቀናት በኋላ ኖኅ ውሃው ከምድር ላይ ደርቆ እንደ ሆነ እንዲያይ ቁራ የተባለን ወፍ/አሞራ ላከ። ቁራው እዚህም እዚያም እየበረረ ደረቅ መሬት ቢፈልግም ሊያገኝ አልቻለም።

በኋላም ኖኅ ርግብ የተባለች ወፍ ላከ። ይሁን እንጂ የምታርፍበት መሬት ማግኘት ስላልቻለች ወደ ኖኅ ተመልሳ መጣች። ከሳምንት በኋላ ኖኅ እንደ ገና ርግቧን ላካት። እርሷም የወይራ ቅጠል በአፏ ይዛ ተመለሰች ውሃው ይቀንስ ስለ ነበር ተክሎችም ደግሞ መብቀል ጀመሩ።

ኖኅ ሌላ አንድ ሳምንት ጠብቆ ርግቢቷን ለሦስተኛ ጊዜ ሰደዳት፤ በዚህ ጊዜ የምታርፍበት ስፍራ ስላገኘች ተመልሳ አልመጣችም። ውሃው ይደርቅ ነበር።

ከሁለት ወራት በኋላ እግዚአብሔር ኖኅን አንተ ቤተ ሰብህና እንስሳቱ በሙሉ ከመርከቧ ውጡ አለው። ቤተ ሰቡ ከመርከቢቱ ወጡ። ብዙ ልጆችና የልጅ ልጆችን ወለዱ ምድርንም ሞሉአት።

ኖኅም ከመርከቢቱ ከወጣ በኋላ መሠዊያ ሠራና ከእያንዳንዱ እንስሳ ለመሥዋዕት ሊቀርቡ የሚችሉትን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አቀረበ። እግዚአብሔርም በመሥዋዕቱ ተደሰተ ኖኅንና ቤተ ሰቡን ባረካቸው።

እግዚአብሔርም አለ። “ሰዎች ስለሚያደርጉት ክፉ ነገር ዳግም ምድርን ፈጽሞ ላልረግማት ቃል እገባለሁ። ምንም እንኳ ሰዎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ኃጢአተኞች ቢሆኑም ዓለምን ዳግመኛ በጥፋት ውሃ አላጠፋም” አለ።

እግዚአብሔር ለቃል ኪዳኑ ምልክት ይሆን ዘንድ የመጀመሪያውን ቀስተ ደመና ሠራ። ሁልጊዜ ቀስተ ደመናው በሰማይ ላይ ይታያል። እግዚአብሔር በዚህ ቀስተ ደመና አማካይነት ለሕዝቡ የገባውን ኪዳን ያሳታውሳል።

Verwandte Informationen

Worte des Lebens - GRN hat Audio-Gospel-Botschaften in tausenden von Sprachen, beinhaltet bibelbasierte Botschaften über die Erettung und das christliche Leben.

Freie Downloads - Hier findet man alle GRN Botschaften, Schriften in vielen Sprachen, plus Bilder und andere verwandte Materialien, verfügbar zum Download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons